በህወሀቱ ጄነራል የሚመራው ደም ያረገዘ የመፈንቅለ መንግስት ውጥን!!
ፋሲል የኔአለም

ከዚህ በተጨማሪ ጄ/ል ክንፈ ዳኘውና ተክልብርሃን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ለማድረግ ደጋፊዎችን ለማሰባሰብ እየተንቀሳቀሱ ነው። አስተባባሪዎቹ ለዚህ እቅዳቸው ማስፈጸሚያ የመከላከያ ታርጋ የለጠፈችውን የጄ/ል ክንፈ ዳኛውን መኪና እየተጠቀሙ ነው። ክንፈ ዳኘው ስልጣኑን ቢለቅም ፣ መኪናው አልተወሰደበትም። መከላከያ መኪናውን ለመሰብሰብ ለምን እንዳልፈገ ግልጽ አይደለም። የደህንነት ሰዎች በዋና ተዋናዮች ላይ ፈጣን እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ እቅዱን እየተከታተሉ ማጋለጥ የተሻለ ነው የሚል ስትራቴጂ እየተከተሉ ነው። የዚህን ስልት አዋጪነት በሂደት የምናየው ይሆናል። በአጠቃላይ ግን የእነ ጄ/ል ክንፈ ዳኘውና ተክለብርሃን እቅድ በራዳር ውስጥ እንደገባ እነሱን ለመከተል ያሰቡ ሃይሎች ቢያውቁት አገራችንን አላስፈላጊ ከሆነ ደም መፋሰስ መታደግ ይቻላል። በተለይ አረናዎች።
በዚህ አጋጣሚ ለስራ ጉዳይ ከአምስተርዳም ወጣ ብዬ ስለነበር የባህርዳሩን ሰልፍ በቀጥታ ለመከታተል እድል አላገኙሁም ነበር። በሁዋላ ላይ እንዳየሁት ሰልፉ እጅግ የተዋጣለትና ታሪካዊ ሰልፍ ነበር። በሰልፉ ላይ የተሳተፉትን ዜጎች ፣ በበጎ ፈቃደኝነት ጥበቃ ሲያደርጉ የነበሩ ከ1 ሺ በላይ ወጣቶች፣ የብአዴን አመራሮችና የደህንነት ሰዎችን ማመስገን ይገባል።