>
5:13 pm - Wednesday April 19, 9769

"የገዱን ቡድን ማሸነፍ ካልቻልን እናፍርሰው" በሚል መርህ እነ በረከት 6 ሚልዮን ብር መድበዋል!!!  (ሚኪ አምሀራ)

“የገዱን ቡድን ማሸነፍ ካልቻልን እናፍርሰው” በሚል መርህ እነ በረከት 6 ሚልዮን ብር መድበዋል!!! 
ሚኪ አምሀራ
ከ 65 አካባቢ የብአዴን ማእከላዊ ኮሚቴ ወደ 26 የሚሆኑት ቀንደኛ የበረከት ደጋፊ እና ለዉጡን አጥብቀዉ የሚቃወሙ ህዋሀትን ከእየሱስ ክርስቶስ በላይ የሚወዱ ናቸዉ፡፡ 6 ወይም 7 አካባቢ የሃይል ሚዛን አይተዉ የሚወስኑ እንዲሁም 3 ወይም 4 ገደማ ከሞተ ሰዉ ማይሻሉ ምንም የሚያዉቁት ነገር እንደሌለ ነዉ፡፡ ከዛ ዉጭ ከዞንና ወረዳ ተመርጠዉ በብአዴን ጉባኤ በመገኘት ለማእከላዊ አባል የሚሆን እጅ እያወጡ የሚጠቁሙ ናቸዉ፡፡ እነ በረከት እና ህላዊ ከብአዴን ጋር እንደማይቀጥሉ ያዉቁታል፡፡ ነገር ግን አሁን ለዉጥ እየፈለገ ያለዉን ቡድን አበላሽተዉ መዉጣት ነዉ የፈለጉት፡፡ ከቻሉ የህወሃት ደጋፊ የሆነዉን ቡድን አሸናፊነቱን ተጎናጽፎ እንዲወጣ ካልሆነ ግን የነ ገዱ ቡድን አፈራርሰዉ ለመዉጣት የሞት ሽረት ትግል ላይ ናቸዉ፡፡፡፡ ህወሃት እኔ የማላዘዉ ቡድን መፍረስ አለበት ነዉ እያለ ያለዉ፡፡ የእነ ገዱ ቡድን ሚዲያዉን ስለያዘ እንጅ ይሄን ተገንዝበዉ እንቅስቃሴ ያደረጉ አይመስልም፡፡ በአንጻሩ በረከት በምስራቅም በምእራቡም የአማራ ክፍል በአካል ከዛም ሲያልፍ በስልክ ብዙ ስብሰባ ላየ ሊገኙ የሚችሉ ሰወችን በማግኘት እነ ማንን መደገፍ እንዳለባቸዉ እነ ማንን መታገል እንዳለባቸዉ አቅጣጫ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ በረከት ወደ 6 ሚሊየን ብር መድቦ ነዉ ይሄን እንቅስቃሴ ከሚያዚያ ጀምሮ የጀመረዉ፡፡ ብሩን በየአካባቢዉ ፕሮጀክት ለመቅረጽ ብሎ ከ አማራ ብድር እና ቁጠባ ተቋም ከእነ መኮነን የለዉም ወሰን (አረቲፊሻል ጸጉር ጭንቅላቱ ላይ ያስተከለዉ ሰዉ) በመመሳጠር ነዉ የወሰደዉ ይባላል፡፡ለእነዚህ ደጋፊ ካድሬወች ብዙ ገንዘብ በትኗል፡፡ በብአዴን ስብሰባ አሸናፊ ሁነዉ ከወጡም እስከ መቶ ሽህ ብር ቃል ተገብቶላቸዋል፡፡
እዚህ ስብሰባ ላይ ማን ማንን እንደደገፈ፤ማንን እንደተቃወመ፤ ከማን ጋር እንደሸረበ እያንዳንዱን የወረዳ እና የዞን አመራር እንዲሁም ክልል ላይ ያሉ ሰወች መረጃ በማዉጣት የበረከትን ቡድን የደገፈዉን አይቀጡ ቅጣት ለመቅጣት እንዘጋጅ፡፡ ስንት የአማራ ልጆች የሞቱበትን ለዉጥ የነዉጠኞች እና የትምህክተኞች ለዉጥ ነዉ እያሉ እየፎከሩ እንዲሁም ባህርዳር ላይ በየሳምንቱ እንደሚሰበሰቡ ሰምተናል፡፡ በዚህ ሳምንት ከጠገዴ ሶረቃ እስከ ራያ ቆቦ፤ዳንግላ፤እንጅባራ ደብርብርሃን ለዉጡን ደግፈህ የወጣህ ወጣት ተዘጋጅተህ ጠብቅ፡፡ የእነ በረከትን ቡድን ደግፎ አጨብጭቦ መርጦ የመጣን የዞን፤ የወረዳ እና የክልል ባለስለጣን በሳለም ሊኖር አንፈቅድለትም፡፡ ይሄን ያረገ ቀን በራሱ እና በቤተሰቡ ላይ እንደፈረደ ማወቅ አለበት፡፡ በሙስና እና የገበሬ መሬት በመሸጥ የገዛዉን ቤቱን ወደ አመድነት እንደሚቀየር እናሳየዋለን፡፡ የበረከት ጉያ ዉስጥ ይገባ እንደሆን ያኔ እናያለን፡፡
Filed in: Amharic