የአቋም ለውጥ
እንደ አብዛኛቹ ተከሳሾች ሁሉ የፖለቲካ የድርጅት አባል ሆኜ አላውቅም። አሁን ግን አቋሜን ቀይሪያለሁ። ታግሎ ሊያታግል በሚችል ድርጅት ተቀልቅዬ ከተራ አባልነት እስከ አመራር አቅሜ የፈቀደለኝን ሁሉ ለማድረግ ወስኛለሁ። ይህንንም የቋም ለውጥ በተግባር እና በይፋ በቅርቡ አሳውቃለሁ። ህዝባችንን የበለጠ አደራጅተንና አስተባብረን መታገል የወቀቱ ታሪካዊ ጥሪ ነው። እኔም አንዳርጋቸው ጽጌ ነኝ! እኔም አሸባሪ ነኝ!
ጋዜጠኛና ኣክቲቪስት ኣበበ ገላው ሜይ18.2012 ለታሰሩት፣ለተገረፉት፣ለተሰደዱት የድምጾች ሁሉ ድምጽ በመሆን የወያኔ ቁንጮን ኣንገት ያስደፋበትን ቪዲዮ ለትውስታ።