>

'' ሕልም አለኝ'' 'ድል ለዲሞክራሲ'! (ሀይለገብርኤል አያሌው)

” ሕልም አለኝ” ‘ድል ለዲሞክራሲ’!
ሀይለገብርኤል አያሌው
የሰላማዊ ትግል አምድ ‘’I Have a Dream ‘’  በሚል የተስፋና የትንቢት ቃሉ የሚታወቀው የጥቁሮች የነጻነት አባት Martin Luther King  Jr ልደት ተከብሮ የሚውልበት   የአሜሪካብሄራዊ በአል  እለት ነው::
ይህ ጀግና ለሕግ ልዕልና ለዜጎች እኩልነት እስከ ሕይወቱ ፍጻሜ በጽናት ታግሎ ታሪክ ጥሎ አልፏል:;
በአለም ላይ ከነገሱ ነገስታትና ሃያላን በላይ ስሙ የገነነ ዘወትር በበጎ ተምሳሌትነቱ ሲወሳ የሚኖር የምድራችን ልዩ ባለዝናና ተወዳጅ የሰላም ሰው ለመሆኑ የሚወዱት ብቻ ሳይሆን የሚጠሉትና ያስገደሉት ጭምር የሚመሰክሩት እውነት ነው:: ማርቲን ሉተር ኪንግ ሕልም አለኝ! በሚለው ዘመን ተሻጋሪ ንግግሩ  አንድ ቀን በዚህች ሃገር የቀለም ልዩነት ጠፍቶ ሰዎች በሰውነታቸው እንደሚከበሩ ተናግሮት የነበረው ትንቢታዊ ቃል እርሱ ባያየውም በቀጣዩ ትውልድ ዘመን  ተግባራዊ ሆኗል:: ሕዝቡም ጀግናውን የማይረሳ ታሪኩንም የማይዘነጋ በመሆኑ ይህው ዛሬ በሕይወት ካሉት የአሜሪካ መሪዎች ልቆ ልደቱ የሚከበር ተጋድሎው ሲዘከርና ሲታወስ ይኖራል::
የኛው እስክንድር የማርቲ ሉተር አድናቂና የትግል ፈለጉን ተከታይ ለሃሳብ ልዕልና ለፕሬስ ነጻነት ለሕግና ፍትህ መረጋገጥ የምቾት ኑሮውን ሕይወቱንና መላ  ቤተሰቡን ትቶ ባለፋት 27 የጭለማ አመታት ይህ ነው የማይባል መራራ መስዋዕትነት ሲከፍል ቆይቷል:: እስክንድር የገጠመው ባላጋራ ማርቲን ሉተር ከታገላቸው  የነጭ የበላይነት አራማጅ ዘረኞች  የባሱ ናቸው ቢባል ማጋነን አይሆንም:: ድንቁርና የበታችነት ስነልቦና የገንዘብ ፍቅር የወረደ ጎጠኝነትና የጥላቻ ስሜት ያደቀቃቸው ከሰው ዝቅ ብለው ከአራዊት የቀረቡ የትግራይ ወንበዴዎች ከ10 ግዜ በላይ በእንበለ ፍርድ ደጋግመው ቢያስሩት ቢያስፈራሩትና ንብረቱን ቢወርሱ ቤተሰቡን ቢያጎሳቁሉ እስክንድር ከያዘው የነጻነነትን የዲሞክራሲ መንፈስ ዝንፍ ሳይል ዛሬ ለደረስንበት አንጻራዊ የነጻነት ቀን አብቅቶናል::
ይህ ወቅት ሲታሰብ ለዲሞክራሲ ለዜጎች እኩልነት ለመብትና ነጻነት የታገሉ ሁሉ የሚከብሩበት:: ስማቸው ከፍ ብሎ የሚነሳበትና ታሪካቸው የሚነገርበት አጋጣሚ ነው:: እስክንድር ባለመሸነፍ አቋሙ በጽናት በቁርጠኝነቱ እና  በትውልድ ተምሳሌትነቱ በኢትዮጵያ የትግል ታሪክ ውስጥ ስሙ ለዘመናት ከፍ ብሎ ሲነሳ ይኖራል:: እስክንድር በትንታግ ጋዜጠኝነቱና በመብት ታጋይነቱ በአለማችን ካሉ ስመጥር ታጋዮች ጎን የተደመረና አለም አቀፍ እውቅና የተቸረ የሰላም አርበኛ በመሆኑም ምሳሌና አዐያነቱም ሌሎች የምድራችን ሃገራት ሕዝቦች የሚጋሩት ባለ ታሪክ ያደርገዋል::
እኛ ኢትዮጵያውያን በተግባራዊ ስራቸው በሃገራዊ አስተዋጽዖቸውና በተጋድሏቸው የምንዘክራቸው ለትውልድ ምሳሌ ለሃገሪቷም አሴት የሚሆኑ የጋራ ብሄራዊ ጀግኖች ልናከብር ይገባል:: ይህ ደግሞ በቅርቡ እንደሚሆን :
” ሕልም አለኝ”
‘ድል ለዲሞክራሲ’!
Filed in: Amharic