>

አክራሪ የኦሮሞ እስላሞችን ለመምከርና ከረሱት ለማስታወስ ያህል ... (ዘመድኩን በቀለ) 

አክራሪ የኦሮሞ እስላሞችን 
ለመምከርና ከረሱትን    ያህል ነው
ዘመድኩን በቀለ 
ምክሩ ኢትዮጵያዊውን ሙስሊም አይመለከትም!!
★ ኢትዮጵያዊውን ኦሮሞም አይመለከትም!!  
★ ምክሩ ባለሜንጫዎችንና እጅ ለመጠምዘዝ ሞካሪዎቹን የሚመለከት ነው። 
★ ይሄኛውም ጦማር ወንድማዊ ምክሬን ያለስስት፣ ያለ ገደብ የለገስኩበት ነው። በጥሞና ስሙኝ። የታጠቃችሁትን ሱሪ የታጠቀ ከዚህኛው ሰፈርም አለ። ለቀረርቶ፣ ለሽለላ፣ ለፉከራም የተሻለ ፎካሪ በዙሪያችሁ አለ። እናም በረድ ብትሉ መልካም ነው። ይሄም ምክሬ ነው።
•••
ወዳጄ እከብባለሁ ስትል መከበብ አለና መጠንቀቁ አይከፋም። አስጨንቃለሁ ስትልም አስጨናቂ ይመጣብሃልና ተጠንቀቅ። አየሩን በሙሉ መቆጣጠሩን ብትተወው ቢቀርብህም ይሻልሃል። ከዓመት በፊት የተወገደው የትግሬ ወኪል ነኝ ባዩ የህወሓት መራሹ መንግሥት በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ህዝቦችን ጨፍለቆ በመግዛቱ የተነሳ መጨፍለቅ የሰለቸው ህዝብ ካካ የነካው እንጨት አደርጎ እንዴት አድርጎ አሽቀንጥሮት እንደጣለው ማስታወሱበይሻልሃል።
•••
ባለተራው። ባለ ጊዜው። ዛሬ የምትመካበትን ዐቢይ አህመድንና ለማ መገርሳን ከህወሓት እስራት የታደገው ዛሬ አፍህን የምትከፍትበት ነፍጠኛው ደመቀ መኮንን ነው። አንተ ሁለት እጅህን አጣምረህ በአግአዚ ጥይት ስትታጨድ የኦሮሞ ደም ደሜ ነው ብሎ በአግአዚ ስናይፐር ጎንደርና ባህርዳር ላይ የተረፈረፈው ዛሬ የሚኒልክ ሰፋሪ እያልክ በቁሙ ቤቱን የምታፈርስበት ዐማራው ነው። ዐማራው ነው ለምን ኦሮሞ ብቻውን ይሞታል ብሎ አደባባይ ወጥቶ ድምጹን እያሰማ አብሮህ የሞተው። ስማ አንት ውለታ ቢስ።
•••
ኦቦሌሶ ህወሓትን ጉባኤ ያስቀመጣት የሀረርጌው የጭናክሰን ዐመጽ አይደለም። የባሌ፣ የአምቦም፣ የነቀምቴም፣ የሞያሌም ሰልፍ አይደለም። ህወሓትን ለለውጥ ያስቀመጣት የጎንደሩና የባህርዳሩ የወንዶቹ ዐመፅና ምላሽ ነው። ህወሓትማ ዐማራው ባይቃወማት ኖሮ ኦሮሞንም ኢትዮጵያንም 100 ዓመት ያለከልካይ ጨብጣ ትገዛ ነበር። እውነቱን ይሄው ነው። ለምን ይዋሻል። እንዋጠው እንጂ። ሞያሌ ላይ 5 ተኩሳ 50 ሺ ኦሮሞ ኬንያ የገባው ትናንት እኮ ነው። ለምን አትከባበሩም። በየትኛውም ዐመፅ ሱዳን የተሰደደ ዐማራ የለም። ዐማራ የሚሰደደው በሀገሩ ነው። ጀግና ነኝ ስላልክና ስለፎከርክ ጀግንነት እንደ መንፈስ አትሞላም። ጀግንነት ከሀቀኞች ጋር ናት።
•••
ጀግና እኮ የገዛ ወገኑ ላይ አይፎክርም። ጀግና ምስኪኖችን አይጨፈልቅም። ጀግና የሰው ንብረት አይቀማም። ጀግና ሁሉ ኬኛ አይልም። ጀግና ሴት አያስለቅስም። ጀግና አቅመደካሞችን በግሬደር አይጨፈልቅም። ጀግና ህጻናትን ሜዳ ላይ አይበትንም። ጀግና ዓይነስውራን ላይ ቤት አያፈርስም። ጀግና ሩህሩህ ነው። ጀግና ለተጠቁ ጠበቃ ነው። ጀግና ሙያ በልብ ነው ባይ ነው። ጀግና ጠላቱን ያውቃል። ጀግና የሚውልበትን ያውቃል። ወዳጄ በአፉ የሚጸዳዳ ሁሉ ጀግና አይደለም።
•••
የጨነቀው ዕለት ይመጣል። እንደተመኛችሁት የፍጻሜው ጨዋታ ይጀመር እንኳ ቢባል ውጤቱ ሳይታለም የተፈታ ነው የሚሆነው። ቡድናችሁ የታወቀ ነው። አቅሙ፣ የሰው ኃይል አሰላለፉ ሁሉ የታወቀ ነው። የቡድኑ ስነልቦናም የታወቀ ነው። ደካማና ጠንካራ ጎኑም የታወቀ ነው። አሰልጣኙም፣ ወጌሻውም የታወቀ ነው።
•••
ግብፅን ከኋላው ያሰለፈ ኃይልና ኢትዮጵያውያንን ከኋላው ያሰለፈ ኃይል እኩል አያሸንፍም። አሁን ሶማሌው አኩርፏል። ጌዲኦው በአክራሪው ኦሮሞ መንግሥት በረሃብ እየተቀጣ ነው። የእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች እንኳ ገብተው የነፍስ አድን ሥራ እንዳይሠሩ እየተደረጉ ነው። ኦሮሞ መራሹ መንግሥት አናሳ የደቡብ ብሔሮችን ከምድረገጽ እያፀዳ ነው። ግልጽ የሆነ የዘር ማጥፋት በኮሬና በጌዲኦ ነገድሸላይ እየተፈጸመ ነው። ወላይታ ጀዋር ባደራጀው ኢጄቶ እየተወገረ ነው። ጉራጌ፣ ዶርዜ፣ ከምባታና ሀዲያም በአክራሪ ኦሮሞ እየተገረፈ ነው። ትግሬ ቢያኮርፍም ኦሮሞው ኦነግ ዐማራን የሚያጠፋለት ስለሚመስለው በሁለት ልብ ላይ ነው። ችግር ቢደርስበትም ዋጥ አድርጎ ጮጋ ብሎ ነው ተቀምጦ ያለው። ይፍጻሜ ጨዋታው የተጀመረ ጊዜ ግን ህወሓት ዐማራን ለመበቀል ከእናንተ ጋር ለመቆም ብትፈልግ እንኳ የትግሬ ህዝብ ከማን ጋር እንደሚቆም ሳይታለም የተፈታ ነው። የአክሱም ጽዮን ልጆቹም ፣ የአልነጃሺ ልጆችም ከማን ጋር እንደሚቆሙ የታወቀ ነው። እናም አክራሪዎች ሆይ ደጋግማችሁ አስቡበት።
•••
ጠቅላይ ሚንስትሩ አፈ ቅቤ ሆደ ጩቤ ኦሮሞ ስለሆነ፣ የመከላከያ ሠራዊቱ አዛዥ ዐማራ ጠል ኦሮሞ ስለሆነ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊሱም ሆነ ከንቲባው ዐማራ ጠል አክራሪ የኦሮሞ ነገድ አባላት ስለሆኑ፣ ኢተወዮጵያን በትኖ አሜሪካ መግባት የሚፈልገው ዐማራ ጠሉ ሃጂ ጃዋር ለጊዜው በግብጽ ገንዘብ፣ በኦህዴድና በኦሮሚያ ባንክ ድጋፍ፣ በኢትዮጵያ መንግሥት የወታደር ጥበቃ ስለሚደረግለት፣ በዚህ ላይ ጠያቂ የሌለው ሚድያ ስላለው፣ ገንዘብም ስላለው ኢትዮጵያውያንን አሸንፋለሁ ብለህ ሚሪንዳ ይቀቀልልን ባትሉም ምክሬ ነው።
•••
በደብረ ዘይት የኢሬቻ በዓል ላይ 4 ሚልየን የኦሮሞ ቄሮ ነበር የተገኘው። ዳውን ዳውን ወያኔ እያለ ሲጮህ ያየነውም ይሄው ቄሮ ነው። ነገር ግን 9 ጥይት በተተኮሰ ጊዜ ያ ሁሉ ሚልየን ቄሮ በ3 ደቂቃ ውስጥ የገባበትን አይተናል። ታሪክም መዝግቦ ያስቀመጠው ሃቅ ነው። ዓድዋ ከዘመተው 11 ጄነራል 9 ኙ ኦሮሞ ነው ብለህ በባዶ ሜዳ እንደምትፎክረው አይደለም። ዓደዋ የዘመቱት ኦሮሞ ሆነው አይደለም። ኢትዮጵያን ብለው፣ ኢትዮጵያዊ ሆነው ነበር። ኦሮሞ የሚለው ቃል እንኳ ያወጣልህ ጀርመናዊ ግለሰብ ነው። ያውም ከዓደዋ ጦርነት መልስ ማለት ነው። እናም የዓደዋን ጀግና የወገኑን ቤት ፣ ንብረት ከሚያፈርስ አክራሪ የኦሮሞ እስላሞች ጋር አታጋባው።
•••
ይሄ ደብረ ዘይት ላይ የተካሄደው ዓይነት ትዕይንት ጎንደር ላይ  ቢሆን ብለህ ገምት፣ ወሎ ወልድያ ቢሆን ብለህ ገምት። ባህርዳር፣ ደብረ ማርቆስ ቢሆን ብለህ ገምት። ሙሉ ሸዋ ቢሆን ብለህ አስብ። ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን እያሰብክ መመለስ ብቻ ነው። ሬሳው አስፓልቱ ላይ ይከመራታል እንጂ እንዲህ ወደ ሰማይ በተተኮሰ የማስፈራሪያ ጥይት ገደል ገብቶ አያልቅም ነበር።
•••
አሁንም ድንበር አትለፉ። አንበሳው የኢትዮጵያ ህዝብ ፊት ላይ እፎከራችሁ ትእግስቱን አትፈታተኑት። ቀይ መስመሩን እያለፋችሁ ነው። ለጊዜው በኦነግ የተዋጠው ኦፒዲኦ ፊት ስለሰጣችሁ ነው መዘባነን ያበዛችሁት። አሁን ሌሎች ፓርቲዎችም በኦፒዲኦ ቅጥ ያጣ ፋሽስታዊ አገዛዝ እያኮረፉ ስለሆነ ወደ አንድ መምጣታቸው አይቀርም። እናም እደግመዋለሁ ሰከን በሉ።
•••
አዲስ አበባን ኦሸርታይም ሰርተህ ተጠቀም እንጂ የምንና ከየት የመጣ ልዩ ጥቅም ነው የምታወራው። የተበደለ ካለ ይካሳል። በዳይ ቢኖርም ኦሮሞን ሲበድለው የኖረው ዐቢይ አህመድና ለማ መገርሳ የሚመሩት ኦፒዲኦ ነው። እናም በዳዮችህን እሽኮኮ ተሸክመህ አዝለህ እየዞርክ በማይመለከታቸው ዜጎች ላይ መሸለሉ ፌር አይደለም ብቻ ሳይሆን ዋጋም ያስከፍልሃል። እናም ቄሮና ቀሬ ወደ ልቦናችሁ ተመለሱ። ወንድማዊ ምክሬ ነው።
ሻሎም !  ሰላም !
የካቲት 29/2011 ዓም
ከራየን ወንዝ ዳር።
Filed in: Amharic