ዮናስ ሀጎስ
የሆነ ከተማ የእኛ ነው የሚሉ ገጠሬዎች ፀባይ በከተማው ተወልዶ ያደገን ሰው ከገጠር መጥተው በገዛ ሃገሩ ህጋዊ በሆነ መንገድም ቢሆን እንዳይንቀሳቀስ ማድረግ ነው። ይህን የሚያደርጉት ከገጠር መጥተው ሳይወደዱ፣ሳይመረጡ እና ሳይፈለጉ የከተማ ስልጣን ላይ የተሳፈሩ ዘረኛ ሹማምንት ዘመዶቻቸውን ተተግነው ነው።
የሰሩትን ከሰሩ በሃላ ታዲያ የገጠር አራዳን የሚመጥን ከተሜን አመት የሚያስቅ ማታለያ ይዘው ይመጣሉ – “ለራሳችሁ ደህንነት ነው” የሚል የገጠር እርድና!
የዛሬው የእስክንድር እግድም ምክንያቱ “አጥፍቶ ጠፊ ጋዜጠኛ ወደ አዳራሹ እንደሚገባ ከተፎው የሃገር ደህንነት መስሪያቤት ከሞሳድ ጋር በጥምር ባደረገው እንቅስቃሴ ስለተገነዘበ ነው” መባሉ አይቀርም፨ “እውነት ነው እስኪ በጎ አስቡ” የሚል ቤተዘመድም፣ወዶ ገባ ተቃዋሚም አይጠፋም!
የመንግስት ክልከላዎች ነገር…
1) እስክንድር ነጋን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ያሉበት አዲስ የሚድያ ተቋም መቋቋምን አስመልክቶ ዛሬ በኢትዮጵያ ሆቴል የተጠራው ጋዜጣዊ መግለጫ በፌደራል ፖሊስ ጣልቃ ገብነት እንዲሰረዝ ተደርጓል። ሰናይ ሚድያ የሚል ስያሜ ለተሰጠው ለዚህ 24 ሰዓት አገልግሎት ስለሚሰጠው የቴሌቭዥን ጣቢያ ጉዳይ ለጋዜጠኞች መግለጫ ለመስጠት የተያዘው ቀጠሮ ለምን ፖሊስ ጣልቃ ገብቶ ሊሰርዘው እንደቻለ ባይታወቅም ቅሉ ይህ ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን የመጣስ ድርጊት በእስክንድር ነጋ ላይ ሲፈፀም ያሁኑ ለሁለተኛ ጊዜው ነው። ከዚህ ቀደምም በራስ ሆቴል እስክንድር ጠርቶት የነበረ ጋዜጣዊ መግለጫ ፖሊስ «ለራሱ ለእስክንድር ደህንነት ሲባል» በሚል ውኃ የማይቋጥር ምክንያት እንደሰረዘው የሚታወስ ነው።