የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በወቅታዊ ሁኔታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መግለጫ
.
በመላው ዓለም የምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በደረሰው ወቅታዊ እና ያልታሰበ ጉዳት በሐዘን ላይ የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናንና ምዕመናት: የኢትዮጵያ እስልምና ጠቅላይ ምክር ቤት እና የመጅሊስ አባላት የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ወገኖቻችን፦
•
በአማራ ክልል በምሥራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ወረዳ በቤተ እምነቶች ላይ የቃጠሎ ጉዳት መድረሱን ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ሰምተናል። በጉዳቱም የተሰማንን ልባዊ ሐዘን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እንገልጻለን።
•
የተፈጸመው ድርጊት የሀገራችን ሰላም እና እድገት የማይጠቅም ለዘመናት የቆየ አብሮነት የመኖር ዕሴቶቻችን የሚንድ መሆኑን መላው ሕዝባችን ተረድቶ በተረጋጋ እና በሰከነ መንፈስ ጉዳዩ እስከሚጣራ በትእግስት እንድትጠባበቁ እናሳስባለን።
•
ከዚሁም ጋር የሚመለከታችሁ የመንግሥት አካላት ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት አስፈላጊው ክትትል እንድታደርጉ እናሳስባለን።
•
ይኽንኑ ድርጊት አስመልክቶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከሚመለከተው የመንግሥት የአስተዳደር :የሕግ እና የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን አጣርተን ይፋ የምናደርግ መሆኑን በአጽንዖት እንገልጻለን።
•
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!!
መ/ር ኃይሉ በላይ
EOTC TV