>

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በወቅታዊ ሁኔታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መግለጫ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በወቅታዊ ሁኔታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መግለጫ

.
በመላው ዓለም የምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በደረሰው ወቅታዊ እና ያልታሰበ ጉዳት በሐዘን ላይ የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናንና ምዕመናት: የኢትዮጵያ እስልምና  ጠቅላይ ምክር ቤት እና የመጅሊስ  አባላት የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ወገኖቻችን፦
በአማራ ክልል በምሥራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ወረዳ  በቤተ እምነቶች  ላይ የቃጠሎ ጉዳት መድረሱን ከተለያዩ  የመረጃ ምንጮች  ሰምተናል። በጉዳቱም  የተሰማንን ልባዊ ሐዘን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እንገልጻለን።
የተፈጸመው ድርጊት የሀገራችን ሰላም እና እድገት የማይጠቅም ለዘመናት የቆየ አብሮነት የመኖር ዕሴቶቻችን የሚንድ  መሆኑን መላው ሕዝባችን  ተረድቶ  በተረጋጋ እና በሰከነ መንፈስ ጉዳዩ እስከሚጣራ  በትእግስት እንድትጠባበቁ እናሳስባለን።
ከዚሁም  ጋር  የሚመለከታችሁ የመንግሥት አካላት ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት  አስፈላጊው ክትትል እንድታደርጉ  እናሳስባለን።
ይኽንኑ ድርጊት አስመልክቶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከሚመለከተው የመንግሥት  የአስተዳደር :የሕግ እና የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን አጣርተን ይፋ የምናደርግ መሆኑን በአጽንዖት እንገልጻለን።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!!
መ/ር ኃይሉ በላይ
EOTC TV
Filed in: Amharic