☞ አባ ገብረ ማርያም፣
☞”ዲያቆን” ኃይለ ሚካኤል ታደሰ
☞ቄስ በዳሳ ቶላ
፩) ከዚህ በኋላ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያንን አይፈጽሙም። ቀድሰው አያቆርቡም፣ መስቀል አያሳልሙም፣ አይባርኩም፣ ንስሐ አይሰጡም፣ አይናዝዙም።
፪) በስመ ማእረጉ አይጠሩበትም። ሁሉም ማእረገ ሥልጣናቸው በመያዙ ሁሉም “አቶ” ሆነው ይቆያሉ።
፫) የክህነት ምልክቶችን አይጠቀሙም። የመባረኪያ መስቀል አይዙም። የስብከተ ወንጌል ቀሚስ አይለብሱም።
☞ ከዚህ ውሳኔ ተላልፈው ቢገኙ ግን ቅጣቱ ወደውግዘት ከፍ ይላል። ቅጣታቸው ወደ ውግዘት ከፍ ካለ ደግሞ የሚያዝባቸው ሥልጣነ ክህነታቸው ብቻ ሳይሆን ከምእመናን አንድነት እና ከቤተክርስቲያን ኅብረትም ይለያሉ።
☞ ከውግዘት በፊት ተመክረው እና ወደልቡናቸው ተመልሰው ለጥፋታቸው ይቅርታ ጠይቀው የበደሏትን ቤተክርስቲያን ክሰው ለመመለስ ፈቃደኛ ከሆኑ ግን የተያዘው ሥልጣነ ክህነታቸው ይመለስላቸዋል። እስከዚያው ግን ከምእመናን እንደ አንዱ ሆነው “አቶ” ሆነው ይቆያሉ።
