![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2020/04/brhanekeskel-300x300.jpg)
ቆንስላ ጄኔራል ዶር ብርሀነ መስቀል ሰኚ ከዲፕሎማቲክ ስልጣናቸው ተባረሩ !!!
![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2020/04/brhanekeskel-300x300.jpg)
ኢትዮ 360
በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄኔራል በመሆን ላለፈው አንድ አመት በለውጡ አስተዳደር የተሾሙት ዶር ብርሀነመስቀል አበበ ሰኚ ከስልጣናቸው መባረራቸውን የዲፕሎማቲክ ምንጮች ለኢትዮ 360 ገለፁ::
ቆንስላ ጄኔራል ዶር ብርሀነ መስቀል ሰኚ ከዲፕሎማቲክ ተልዕኮአቸው ባፈነገጠ መልኩ ፅንፈኛ የኦሮሞ ብሄርተኛ ፅሁፎችን በማህበራዊ ሚዲያ በማስተጋባት እና በዘረኝነታቸው ይታወቃሉ::
ዶር ብርሀነመስቀል ስኚ ከሀላፊነታቸው መነሳታቸውን የፃፈው የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የሰው ሀብት ልማት ፅህፈት ቤት ሲሆን አምባሳደሩ እስካሁን ላገለገሉት ጊዜ ምስጋና ከማቅረብ ውጭ የተባረሩበትን ምክንያት አልገለፀም::ሌላ ቦታ ስለመመደባቸውም ያለው ነገር የለም::
ይህም ሆኖ ግን አምባሳደሮች በአዲስ አበባ ስልጠና ሲወስዱ በማጠቃለያው ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ አንዳንድ ዲፕሎማቶች ከተሰጣቸው ሀገራዊ ተልዕኮ ይልቅ የብሄር አጀንዳ የሚያስተጋቡትን በስም ሳይጠቅሱ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበው ነበር::
ዶር ብርሀነ መስቀል ግን ብሄር ተኮር እና ፅንፈኛ ፅሁፎችን ከማውጣት እንዳልተቆጠቡ መረጃዎች ያመለክቱ እንደነበር የኢትዮ 360 ዲፕሎማቲክ ምንጮች ገልፀዋል::
እናም በአቶ ገዱ እንዳርጋቸው የሚመራው የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር በአቶ ብርሀነመስቀል ላይ እርምጃ ለመውሰድ መገደዱን ምንጮች ጨምረው ገልፀውል::
በካሊፎርኒያ ሎስአንጅለስ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄኔራል የነበሩት ዶር ብርሀነመስቀል ሰኝ በቀድሞው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዶር ወርቅነህ ገበየሁ በአቶ ለማ መገርሳ ጎትጏችነት ሹመቱን እንዳገኙ ይነገራል:: ዶር ብርሀነመስቀል ሹመቱ ሲሰጣቸው አክቲቪስት እንደነበሩ እና የአሜሪካ ዜግነታቸውንም እንደያዙ መሆኑም አይዘነጋም::
አምባሳደር ብርሀነመስቀል ከሃላፊነት መነሳታቸውን በተመለከተ እርሳቸውን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም::