>
11:17 am - Saturday June 3, 2023

አብይ ጉንዳናቸው...!!! (በእውቀቱ ስዩም)

አብይ ጉንዳናቸው…!!!

በእውቀቱ ስዩም

“…ጠቅላያችን አንድ ሚሊዮን ጉንዳን ተሸክሜ ነው ያለሁት…” ሲሉ ሰማሁልበል? ለመሆኑ አንድ ሚሊዮን ጉንዳን ስንት ኪሎ ይመዝናል?…
ብቻ አያድርስ ብዬ ልለፈውና …
ከሁለት አመት በፊት” በሰላም  አውለኝ “ የሚል ጥቅስ ግንባሩ ላይ የለጠፈ የህዝብ አውቶብስ አቃጥሎ ፤ በፖሊስ ተይዞ” ለምን እንዲህ አደረግህ ሲባል” ሰላም ባስ” መስሎኝ ነው” ያለው ጎረምሳ  አሁን የወያኔንና  እና የወነግን ባንዲራ  ደርቦ ይዞ  ፎቶ ሲነሳ ታየዋለህ!
 “ገብቶት ነው ? አውቆት ነው? በድለነው ነው?” አለ መንግስቱ ‘ማረ ፋከ ‘ ሃይለማርያም!
ኢትዮጵያ ውስጥ የደረሰው ግድያና ውድመት በጥፍራም  ብሄርተኝነት ጦስ ምክንያት  የመጣ ቢሆንም መንግስትም ከተጠያቂነት አይድንም፤ በቸልታም ሆነ ባቅመቢስነት የህዝቡን ደህንነት የማስጠበቅ አቅም እንደሌለው ተባኖበታል፤አሁን  ደሞ ‘የጨዋ ልጅ ካፈረ በግ ከበረረ አይመለስም ‘ ሆኖበት የከርቸሌ  ዙሩን አክርሮታል!   ለመሆኑ   ቤትሄለም ታፈሰ  ምን አድርጋ ነው የታሰረችው?    በዚህ አካሄድ ኩኩ ሰብስቤንስ መች እንጠብቅ?
ስሙማ ቅድም ዩቲውብ ላይ “ ተቀበል ቁጥር አራት “ የሚለውን ዘፈን ሳዳምጥ ከሁለት አመት በፊት የነበረውን አንጀባችን ትዝ ብሎኝ ሳቅሁ፤
“ደመቀ አገሩ ገዱ ቢቀናቸው
የለማ ሆነና አቢይ ጉዳያቸው “
ይላል ዘፋኙ!
አቤት ! ወግ ወጉንኮ ይዘነው ነበር፤
አሁን ግጥሙን ትንሽ ማስተካከል የሚያስፈልግ ይመስለኛል፤
“ደመቀ አገሩ ገዱ ቢቀናቸው
የለማ ነገር ነው አቢይ ጉንዳናቸው ፤
ለማንኛውም፤
Abiy must go  forward:-)
Filed in: Amharic