>
5:13 pm - Friday April 18, 4352

 "ወሬያቸውን ሳይሆን ተግባራቸውን ያስተዋለ  የምንመራው በዘረኞች እና በናዚዝቶች መሆኑን ይረዳል !!!" (አቶ ፋንታሁን ዋቄ የስነልቦና አማካሪ)

 “ወሬያቸውን ሳይሆን ተግባራቸውን ያስተዋለ የምንመራው በዘረኞች እና በናዚዝቶች መሆኑን ይረዳል !!!”

አቶ ፋንታሁን ዋቄ የስነልቦና አማካሪ

* 10 ሺህ ክርስቲያን ተፈናቅሎ ከ 200 በላይ ታርዶ ለአንድ ሰው ቤተሰብ ማቋቋሚያ እና መታሰቢያ ማቆም ላይ ትኩረት መደረጉ ተገቢ አይደለም !
 
* ይሄንን ሰውን ከሰው ለይቶ ማክበር የፖሊሲ መዛባትን ብቻ ሳይሆን የመሪዎቻችንን ስብዕና እና የአይምሮ ጤንነት አጠራጣሪ ያደርገዋል !
የምንመራው በዘረኞች እና በናዚዝቶች ይመስላል ለልጃችን እና ለወንድማችን ለሀጫሉ የወርቅ ኃውልት ልስራ የሚል መንግስት ለፖለቲካ ትርፍ የሟቹን ቤተሰብ በዘለቄታዊነት ለማቋቋም የተንቀሳቀሰው መንግስት ለሌሎች ክርስቲያኖች የማይገደው እስከመቼ ነው? መንግስት ለሀጫሉ የሚያደርገውን ሁሉ አንድም ሳያጓድል ለሌሎችም ማድረግ ግዴታው መሆኑን ማወቅ አለበት የ ሁለት ሙቶ መታረድ እና የ አስር ሺዎች መፈናቀል አንድም ሳይገዳቸው ስለ አንድ የሰው ልጅ ክብር መሆኑ ቀርቶ ትኩረታቸው ለፖለቲካ ትርፍ የሀጫሉን ሞት ይናጠቁታል ።
የአርቲስቱ ግድያ የፖለቲካ መጠቀሚያ ሆኗል ክርስቲያኖችን ከኦሮሚያ ክልል የማፅዳት የጅምላ ጭፍጨፋ ፕሮጀክት ታሪካዊ አመጣጡ በዘር ፖለቲካ ጀርባ በታዘሉ የወሀቢያ አክራሪዎች በጀርመን የግዕዝ ስልጣኔ እና የኦርቶዶክስ ጥልቅ ስነመለኮት አስተምህሮ ቀናተኞች በአውሮፓ ቀኝ ገዢዎች እና በዛሬዎቹ ሀያላን ደባ ተወሳስቦ የተጠመቀ መርዝ ነው ዛሬ በኩሽ እና ሴም የናዚዎች ሀሰተኛ ትርክት እና ስሁት የፖለቲካ ሀሎት በዲሞግራፊ ቀያሪነት ፕሮጀክት ታቅፈው በከንቲባነት በፀጥታ እና የፍትህ መዋቅር ውስጥ ተሰግስገው በመንግስት በጀት የሚንቀሳቀሱ ነፍሰ ገዳዮች የሚመራ አደገኛ የጥፋት ማህበር ነው ።
እነዚህ በክፉዎች እርኩሳን መናፍስት ማደሪያነታቸው ልዩ ፀባይ ያበቀሉ ባለስልጣናት እና የፖለቲካ መሪዎች የዋሁን የኦሮሞ ወጣት ወደጥፋት መሳሪያ በመለወጥ አንገት መቁረጥ አይን መጎልጎል አስክሬን መጎተት ይህንን አይነት ከስብዕና የሚያዋርድ ግብር ያለማምዱታል የኢትዮይያ መንግስት ባለስልጣናት እና የቤተ እምነት ምንደኞችም ይሄንን ርኩሰት ለማስቆም ወኔ እንዳጡ በጎሳ እና በጎጥ በማንነትና በፍቅረ ነዋይ ደንዝዘዋል ሲሉ ትችታቸውን ሰንዝረዋል እርዳታ ወይንም መልሶ ማቋቋም የመንግስት ግዴታ ነው የኛ የጤናማ ዜጎች ዋነኛ ተግባር ዋስትና የሚያረጋግጥ ንቅናቄ ፈጥሮ ዘለቄታዊ መፍትሄ ማስገኘቱ ነው በስርአት እና በመዋቅር የሚፈፀመውን ክርስቲያንን የማፅዳት ዘመቻ ፓስታ እና መኮረኒ በመስጠት በመሰብሰብ ህዝብ በማዘናጋት የወንጀሉ አካል እንዳያደርገን እንጠንቀቅ ።
 በክርስቲያኖች የሚሰበሰበው ገንዘብ ለህግ እና ለአለማቀፍ የጄኖሳይድ መከላከል እንጂ ለፓስታ መግዣ እና ለሌላ ዙር እልቂት እና መፈናቀል ህዝቡን የሚያዘናጋ የ NGO አይነት ህመም ማስታገሻ እንዳይሆን ከፍተኛ ስጋት አለኝ በስቃይ ላይ የሚገኙትን ክርስቲያኖች መንግስት መልሶ እንዲያቋቁማቸው ከሀገር አቀፍ እስከ አለም አቀፍ ንቅናቄ ማድረግ ይገባል በተያያዥነት ትኩረት መደረግ ያለበት በፀጥታ በፍትህ በፖለቲካ መዋቅር እና መሳተፍ እና መቃናት የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ መሳተፍ ክርስቲያን የሚታደን አውሬ ነው ብሎ የሚያምን መንግስት ከሆነ ከቀበሌ ክልል እና እስከ ፌደራል መዋቅሩ ውስጥ የተሰገሰጉትን ፀረ ክርስቲያን ISIS እና የዘር ደዌኛ የናዚ ልጆችን በጤናማ ሰዎች እንዲተካ ለማድረግ የቤተክህነትን አካላት ጨምሮ ሁሉም ዜጋ እንዲንቀሳቀስ ጥሪያቸውን አቅርበዋል ።
Filed in: Amharic