>

የብርሃኑ ነጋ ተቃርኗዊ የፖለቲካ - የአስተሳሰብና የማንነት ቀውስ!!! (ጋዜጠኛ ምናላቸው ስማቸው)

የብርሃኑ ነጋ ተቃርኗዊ የፖለቲካ – የአስተሳሰብና የማንነት ቀውስ!!!

ጋዜጠኛ ምናላቸው ስማቸው

* “አማራ መጤና ሰፋሪ ነው”
በአማራ ላይ የተፈፀመ የዘር ማጥፋት ወይም ጭፍጨፋ የለም” ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
በአሁኑ ምርጫ የብርሃኑን ፓርቲ ከመምረጥ ብልፅግናን መምረጥ ይሻላል፤ ምክንያቱም ሁለቱም ያው ስለሆኑ የስም እንጂ የግብር ልዩነት የላቸውምና !
በአንድ ወቅት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ወደ ቢሮ መጥቶ የኢሳት ጋዜጠኞችን ማነጋገር እፈልጋለሁ ብሎ ሰበሰበን::
ብርሃኑ ነጋ “በኢሳት አሰራር ላይ የግሌን አስተያየት ለመስጠት እፈልጋለሁ “በሚል ገለልተኛ መስሎ የጠራው ስብሰባ ነበር::
ስብሰባው ሲጀመር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢሳትን የወቅቱ አሰራር በመተቸት ተቋሙ በዚህ ከቀጠለ በ6 ወራት  ውስጥ ሊዘጋ እንደሚችል  በማስፈራራት ዛተብን::
ይህም የኢሳቱን የዲሲ ቢሮ ለመዝጋት የነበራቸውን ሴራ በገደምዳሜ እየነገረን ነበር::
በዚህ አጋጣሚ “በላ ልበላሃ ” በተሰኘው የኔ ፕሮግራም ላይ ስለሚቀርቡ ሰዎች አሉታዊ አስተያየት መስጠት ጀመረ::
ከነዚሁም መካከል :-
1- አቶ ያሬድ ጥበቡ
2-ዶ/ር ፍስሐ እሸቱ እና
የመሳሰሉ ሰዎች ለምን ኢሳት ላይ ታቀርባላችሁ ?  በማለት ወደ እኔ እያየ ቅሬታውን ለመግለፅ ሞከረ:: በውቅቱ እነዚህን ሰዎች ያቀረብኩት እኔ ነበርኩ::
በጣም ገረመኝና ” ለምን ? ” የሚል ጥያቄ አቀረብኩለት:: በደፈናው “የሚረቡ ሰዎች አይደሉም “በማለት መለሰልኝ::ለጥያቄየ የሚያረካ መልስ ስላልሰጠኝ ደግሜ ማብራሪያ ጠየቅኩት::
ኢሳት ነፃ ሚዲያ በመሆኑ የፖለቲካ ሰዎችን አመለካከት ማስተናገድ እንጅ ” ለምን እኛ እንፈርጃቸዋለን ” ስል ርእስ ከፈትኩ:: “እንደምትላቸው ከሆኑም አይረቡም ማለት ያለበት አድማጭ ተመልካቹ ነው እንጅ እንዴት ሚዲያ ላይ አታቅርቡአቸው ይባላል ” ስልም ተከራከርኩ::
ለዲሞክራሲ እና ለነፃነት የሚታገል ሚዲያ ለምን በሰዎች ላይ ገደብ ይጥላል? አንተስ እንዴት እንዲህ ልትል ቻልክ እያልኩ አከታትየ ጠየቅሁት::
 “ለዲሞክራሲና ለነፃነት እታገላለሁ እያልክ አፈናን እንዴት ታበረታታለህ ” በሚል ስሜት ነበር ዶር ብርሃኑን የጠየቅኩት ::
በዚሁ አጋጣሚም ዶ/ር ታየ ወልደሰማያትና አቶ ልደቱ አያሌው በኢሳት ላይ ኢንተርቪው ማድርግ ፈልጌ እነሲሳይ አጌና  እንዳልፈቀዱ ነገርኩት::
ዶር ብርሃኑ ገልመጥ እና በስጨት ብሎ “ጭራሽ እነሱንም ልታቀርብ ፈልገህ ነበር? “በሚል ስሜት ርዕሱን ጨርሶ ለመቀየር ሞከረ::
መልሱን እንደምጠብቅ በማሳወቅ ሁሌም እንደምለው  “ጉዳዩን እንደ ቅድመ ምርመራ (Sensorship) ወይም አፈና አድርጌ እንደምቆጥረው አስረግጬ ተናገርኩ::
ዶር ብርሃኑም ምንም ትኩረት ያልሰጠው በመምሰል ” በነገራችን ላይ ሰዎቹ ስለማይረቡ ነው እንጅ አመለካከታቸውን ፈርቼ አይደለም” በሚል ሊያድበሰብሰው ሞከረ:: ሰዎቹን የሚጠላው ግን የፖለቲካ ባላንጣዎቹ አድርጎ ስለሚቆጥራቸው መሆኑ ገብቶኛል::
ወዲያውኑም ስለ ዶር ብርሃኑ ማሰላሰል ጀመርኩ:: ቀደም ሲል “የኢትዮጵያ ሀገራዊ ንቅናቄ ” ብሎ በመሰረተው ስብስብ  ውስጥ ከኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር /ኦዴግ / እና ከአፋር ነፃነት ፓርቲ መሪዎች ጋር እየተፈራረመና እየተላላሰ ” የአማራ ተወካዮች ግን ብሄርተኞች ስለሆኑ መጋበዝ የለባቸውም ” ማለቱን
አስታወስኩ::Double standard!!
እኔንም በተመለከተ በአሉባልታ የሚሰማውን  ይዞ “የአብን ተወካይ ነውና ተጠንቀቁት ” እያለ ለኢሳት ማኔጂንግ ኤዲተሮች መመሪያ እንደሚሰጥ አውቅ ስለነበር  በወቅቱም ፀረ አማራነቱን መገንዘብ ችየ ነበር:: በዚያ ስብሰባችን  ጊዜ ደግሞ ዶር ብርሃኑ ፀረ ዲሞክራቲክ አመለካከት እንዳለው ተገነዘብኩ::
በወቅቱ በነበረው አጋጣሚ ስለ ብርሃኑ ነጋ ማንነት በደንብ እንድገነዘብ አደረገኝ:: ሰውየው እውነትም ፀረ አማራ እና ፀረ ዲሞክራሲያዊ  መሆኑን::
ያኔ በውስጤ የተሰማኝ  ” ይህ ሰው ለኢትዮጵያ ነፃነት እታገላለሁ እያለ ለካ ለስልጣን የሚቋምጥ ሰው ነው ?” የሚል ነበር::
“እንዴት እንዲህ አይነት ሰው ይህን አመለካከት ይዞ ሀገር ሊመራ ይችላል ? ” በሚልም በፊት ስለሱ የነበረኝን በጎ አመለካከት በመቀየር ውድቅ አደረግኩት::
በዚህ አጋጣሚ በሱ ላይ የተሳሳተ በጎ ምስል ይዛችሁ “ብርሃኑ ” ኢትዮጵያን ሊያድን ይችላል “ብላችሁ ለምታስቡ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቼ አንድ ቁምነገር ልንገራችሁ::
በአሁኑ ምርጫ የብርሃኑን ፓርቲ ከመምረጥ ብልፅግናን መምረጥ ይሻላል:: ምክንያቱም ሁለቱም ያው ስለሆኑ ልዩነት የላቸውምና ::
እውነት እውነት እላችሁአለሁ
 “ብርሃኑ ነጋ ለወንበር የቋመጠና ዘጠኝ ፓርቲ የቀያየረ የስልጣን ጥመኛ ስለሆነ ሀገርን አይጠቅምም:: – አትምረጡት!!!
“አማራ መጤ ነው ! አማራ ሰፋሪ ነው
አማረ በዘሩ ተለይቶ አልተጨፈጨፈም ” የሚል ቀጣፊን በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ላይ ማየት አንፈልግም::
Filed in: Amharic