>

አይነኬዎቹ አውዳሚዎች…!!! (ዘመድኩን በቀለ)

አይነኬዎቹ አውዳሚዎች…!!!

ዘመድኩን በቀለ


“…መጀመሪያ ኦሮሙማን አምነህ ትቀበላለህ። በመቀጠል የጅማው ወሄ ኡስታዙ አህመዲን ጀበል የጥፋት መንፈሱን አምጥቶ ይሞላብህና ያጠምቅሃል። ከዚያ እንዳሻህ ትሆናለህ። ትፈነጫለህ። ታሸብራለህ። ታወድማለህ። ታስወድማለህ። ወዳጄ ከዚያ በኋላ አንተን ጫፍህን የሚነካ አንድም የሕግ አንቀጽ ተፈልጎ አይገኝም። አይኖርምም። ለዚህ ሁሉ ግን በመጀመሪያ ከሁሉ አስቀድመህ ስልጤም ሁን ዐማራ የፈለከውን ሁን አስቀድመህ በኦሮሙማ ማመን፣ አምነህም መጠመቅ አለብህ። ከዚያ አለቀ።

“…በትናንትናው ዕለት ብቻ አክራሪና ፅንፈኛ የስልጤ፣ የኦሮሞና ከዐማራ ክልል ከሰሜን ሸዋ ከኦሮሚያ ልዩ ዞን እና የወሎ ኅብረት አባላት የዒድ በአልን ለማክበር በሚል ሰበብ ወደ ስቴድዮም በመሄድ በመስቀል አደባባይ ዙሪያ የሚገኙትን ሃገር ሃብትና ንብረት ዶግ ዐመድ አድርገው አውድመዋል። አላህ ወአክበር እያሉ የሰው ሃቅ፣ የሰው ንብረት፣ የሰው እንጀራ ላይ የክፋት ሰገራ ለቅልቀዋል። በዚህ መንገድ የፈጣሪ የአላህ ታላቅነት እየተነገረ፣ በዓመት አንድ ጊዜ በሚመጣ በዓላቸው ላይ ከዚህ በታች የሚገኙ የህዝብናጰ የመንግሥት ንብረቶችን አውድመዋል።

1፦ ሃዲያ ሱፐር ማርኬት፣

2፦ የኢዜማ ቢሮ፣

3፦ የውጭ ግንኙነት ኢንስቲትዩት፣

3፦ ሲንቄ ባንክ፣ (በስህተት)

4፦ የወጋገን ባንክ 2 ብራንቾች፣

5፦ ወጋገን ባንክ ኤቲኤም፣

6፦ የኢትዮጵያ መድኅን ድርጅት፣

7፦ rendez – vous፣ LA patissere cafe፣

8፦ ቤልሞን ካፌ፣

9፦ ሰማዕታት መታሰቢያ ሙዚየም ከሁለት መኪናዎቹ ጭምር፣

10ኛ፦ ከቦሌ ወደ ስታዲየም ያለው እካፋይ የመንገድ ብረት፣

11ኛ፦ የመስቀል አደባባይ የተወሰኑ መቀመጫ ወንበሮች፣

12ኛ፦ የመስቀል አደባባይ ፖርኪንግ መግቢያ፣ በመስታውት የተሠራ ቤት ሞደን ሴራሚክ፣

13ኛ፦ ብሔራዊ የጀግኖች ሕጻናት አምባ፣

14ኛ፦ ኢትዮ ባስ ትኬት ቢሮ፣

15ኛ፦ ዓባይ ባስ ትኬት ቢሮ፣

16ኛ፦ የመስቀል አደባባይ የትራፊክ ማረፊያ

17ኛ፦ የመስቀል አደባባይ ፖሊስ ኮሚኒቲ ቢሮ

18ኛ፦ ፈረሰኞች ህንፃ እና ሌሎችንም የሰው ሃቆች አውድመዋል። ሌሎች ቅን ሙስሊም አባቶች፣ ወንድሞች፣ እህቶች ፅንፈኞቹን ቢለምኗቸውም፣ ቢማፀኗቸውም ፅንፈኞቹ ፅድቃቸው በማውደም ላይ የተመሰረተ ነውና ይህንኑ ፈፅመዋል።

“…በዚህ ድርጊታቸው ኣላህ የሚደሰት አይመስለኝም። በፍፁም። ከአጋንንት በቀር በዚህ ክፉ ድርጊት የሚደሰት አንድም ኃይል አይኖርም። ብዙ ቤተሰቦች ያዝናሉ። በዚህ ኢኮኖሚው በወደቀበት ዘመን ጥጋበኞቹ

ይህን ሁሉ ፈጽመው እንዳሻቸው ይፏልላሉ።

“…ባለፈው የጥምቀት በዓል ታቦት አላስገባ ያሉትን ኦርቶዶክሳውያን አናት አናታቸውን በጥይት ይበረቅስ የነበረው፣ ብረት ለበስ ተሽከርካሪ ይዞ መጥቶ ለቄሮ ያግዝ የነበረው ፅንፈኛው የኦሮሚያ እስላማዊ መንግሥት በትናንትናው የዒድ በዓል ላይ ያሳያው ትእግስት የጻድቁ ኢዮብን ትእግስት የሚያስንቅ ነበር። ፌደራሎች ሲቀጠቀጡ፣ ሲወገሩ፣ ሲደበደቡ፣ ሲፈነከቱ እንኳ ራሳቸውን ለመከላከል እንኳ አይፈልጉም ነበር። እንደ ባህታዊ፣ እንደ ሐዋርያ ነበር ያደረጋቸው። አሹ…

“…ይሄ የዐብይ አሕመድ ሀሰን፣ የአደም ፋራ፣ የደመቀ መኮንን ሀሰን ዘመን ልክ እንደሌሎቹ ዘመናት ያረጃል ይሞታል። ይለወጣልም። ስልጤ ግን የክርስቲያን ሱቅ ተከራይተህ፣ ሚልዮን የክርስቲያን ደንበኞች ይዘህ እንዲህ መፏለል ልክ አይደለም። ህወሓት ሄዳለች፣ በናለች፣ ጠፍታለች፣ ይሄኛውም የጊዜ፣ የዘመን ጉዳይ ነው። አሽከርነት በልኩ ቢሆን ይመረጣል። አይመስልላችሁም።

“…ለማንኛውም ለዐማራ የታቀደው፣ በመላ ኢትዮጵያም ታስቦ ሲሠራበት የቆየው የወድመት እና የነውጥ ድግስ ባለመናበብ ሰበብ ከሽፎባቸዋል። አሁን ከኢድ በኋላ ወታደራዊ ሥልጠና ወስደን ኦርቶዶክስን አጥፍተን አብያተ ክርስቲያናትን ወደ መስጊድነት እንለውጣለን ያሉትን ፎልፏላ መቃብር ላይ የበቀለ ጫት ቅመው በደሴ ሲለፈልፉ የከረሙትን ፅንፈኞች መጨረሻ ማየት ነው።

“…እየታዘባችሁ…!!

Filed in: Amharic