>

ለፋኖ እስረኞች ቦታ እንዲለቁ የህወሀት እስረኞች በፖለቲካዊ ውሳኔ እየተፈቱ ነው...!!! (ግርማ ካሳ)

ለፋኖ እስረኞች ቦታ እንዲለቁ የህወሀት እስረኞች በፖለቲካዊ ውሳኔ እየተፈቱ ነው…!!!

ግርማ ካሳ


*…. ሌተና ኮሎኔል ሰጠኝ ካሳዬ: ሌተና ኮሎኖል ፍፁም አብርሃም:  ሻለቃ ዋልታንጉስ ተስፋውና ሻለቃ ክንድያ  ግርማይ ጨምሮ በርካቶች ከሜቴክ ጋር እንዲሁም ከህወህት ጋር ከተደረገው ጦርነት ጋር በተገናኘ  ታስረው የነበሩ እንዲፈቱ ትእዛዝ ከአራት ኪሎ ተሰጥቷል:::

ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ፍርድ ቤት ለይስሙላ አለ ይባላል  እንጂ ፍርድ ቤቱ በኦህዴድ ፕለቲከኛ ሹመኞች የተሞላ አብዛኞቹ ዳኞች የኦህዴድ “አባላት”  እንደሆኑ ይታወቃል::

ስለዚህ አብይ አሀመድ ፍቱ ሲል ይፈታሉ : አትፍቱ ሲል አይፈቱም::

ምን አልባትም ደግሞ አሁን ተራው ፋኖዎች የአማራ አክቲቪስቶችን ማሰር ስለሆነ እስር ቤቶች ስለሞሉ ቦታ ለማስለቀቅ ይሆናል::

ማንም ያለ ወንጀሉ መታሰር የለበትም:: የታሰረ በቶሎ ጉዳዩ ታይቶ ወንጀል እንዳለበት ካልተረጋገጠ መለቀቅ አለበት:: በፍርድ ቤት::ቀደም ሲል የትግራይ ወገኖች በጅምላ ሲታፈኑ  ስቃወም የነበርኩ ሰው ነኝ::

አሁን  እስረኞች የተፈቱት በፍርድ ቤት አይደለም: በፖለቲካ ውሳኔ ነው:: ነገ አብይ አህምድ መልሶ ሊያስራቸው ይችላል::

Filed in: Amharic