>

የአማራ ህዝብ እውነቱን ተቀበል !! (ሀብታሙ አያሌው)

የአማራ ህዝብ እውነቱን ተቀበል !!

          ሀብታሙ አያሌው


ማስታወሻህን ተመልከት ጥቅምት 22/2013 ዓ/ም ወለጋ ጉሊሶ  ዘግናኝ ጭፍጨፋ ተፈፅሞ ፓርላማ ውስጥ መቆጣጠር አቅቷቸው በእንባ የተራጩ ነበሩ።  “ጠቅላዩ ተገኝቶ ምላሽ ካልሰጠ በሌላ ማንኛውም ጉዳይ አንነጋገርም” በሚል ቁርጥ አቋም ተያዘ፤ መከላከያ ኦነግ ሸኔ አቅቶት ከሆነ ይነገረን ፣ ህዝባችን ታጥቆ ራሱን ይጠብቅ ተባለ…”

ማህበራዊ ሚዲያው ተናወጠ፣ አማራ ክልል ከፍ ያለ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ…”አብይ ኦነግ ነው፣ አራጃችን እራሱ ነው፣ ለአለም አቀፍ ፍርድ ቤት ይቅረብ” የሚሉ መፈክሮች ተሰሙ… ወዲያው …

ዐብይ አህመድ 5 ቢሊዮን ብር ባጀት ብሎ በካሽ በአንቶኖቭ ወደ ትግራይ ላከ፣ ከደብረጽዮን ጋር በስልክ መወያየቱም ተገለፀ።  በማግስቱ የጉሊሶው የአማራ ጭፍጨፋ ፋይሉ ተዘግቶ የሰሜኑ ጦርነት ፈነዳ ተባለ… አራጅ እና ታራጅ በጋራ እንዝመት ተባለ … ሰሜን ወደመ።

አሁንም ተመልከት… ኦሮሚያ ወለጋ ጊምቢ ከ3ሺህ በላይ  አማራ እንደ አውሬ ተጨፈጨፈ፣ በማግስቱ የብአዴን ዜና  ህወሓት በቆቦ በኩል ወታደራዊ እንቅስቃሴ ጀመረ የሚል ሆነ…  አራጅ ፣ አሳራጅ ፣ ሽፋን ሰጪ የሚጫወቱብህ ለምን ይመስልሃል ??   የኔ ምላሽ አጭር ነው  “ብአዴን በሚባል ትርፍ አንጀት” ስለምትመራ ነው።  ቀዳሚ ትግልህን ከብአዴን ጋር አድርገህ እሱን ከመነገልክ ሌላው እዳው ገብስ ነው።

       አከተመ።

Filed in: Amharic