>

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ዋስትና ታገደ!

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ዋስትና ታገደ!


ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ከእስር እንዲፈታ ወይም የማይፈታበትን ምክንያት ካለ ችሎት ቀርቦ እንዲያስረዳ ታዞ የነበረው አዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን ዛሬ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 1ኛ ፀረ ሽብር ችሎት ቀርቦ፣ የዋስትናው ብይን በፌደራሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት የታገደ ስለሆነ ሊፈፅም ያለመቻሉን አስረድቷል።

ችሎቱም ያልተፈታበትን ይሄን የጠቅላይ ፍ/ቤት ምክንያት ተቀብሎ አሰናብቶናል።

በዚህ መሠረት ጠቅላይ ፍ/ቤት፣ ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ዋስትና ሊፈታ አይገባም ክርክር ላይ ይግባኙን ለማድመጥ ለሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ቀጠሮ የያዘ መሆኑ ታውቋል።

Filed in: Amharic