>

መጅሊስ የቀደምት የሱፊይ ኡለሞች ደም ተፍተው አጥንታቸውን ከስክሰው ያቋቋሙት የሙስሊሙ ተቋም ነው!! (ፈይሰል ሙሳ)

መጅሊስ የቀደምት የሱፊይ ኡለሞች ደም ተፍተው አጥንታቸውን ከስክሰው ያቋቋሙት የሙስሊሙ ተቋም ነው!!

ፈይሰል ሙሳ


ለዘመናት ሙስሊሙን ከፍ አድርገውና ሀገራቸውን አስከብረው ዳር ድንበሯል ጠብቀው ለሀገር ሰላም የቆሙ ከወራሪ ሀይል ደማቸውን አፍስሰው አጥንታቸውን ከስክሰው ሀገራቸውን የጠበቁ ለእምነታቸው ሲሉ በ አፄዎች ግፍ ፍዳቸውን በልተው ዲናቸውን ጠብቀው ያቆዩ ፣ ተበደልን ብለው ለሀገራቸው ጀርባ ሳይሰጡ ፣ ሁለተኛ ዜጋ ሆንን ብለው ሳያለቅሱ ፣ በሀገር መደፈር ቁጭት የተብሰለሰሉ ጎራ ሳይለያቸው ታጥቀው የተዋጉ የነባሩ እስልምና የሱፊ ተከታዮች ዋጋ ከፍለው ባቋቋሙት መጅሊስ ውስጥ ከ 90% በታች ድርሻ ሊቀበሉ አይችሉም!!

ለሀገር ሰላም ስጋት የሆነውን አሸባ^ሪው የውሀብያን ቡድን ከ ሀገር ወዳድ ሱፊዮች እኩል ትከሻ ለትከሻ ለማለካካት መሞከር ታሪካዊ ስህተት ነው!!

በእርግጥ ለሃምሌ 11 የሸራተን ስብሰባ በኛ በኩል መስራት ያለብንን የቤት ስራችንን ጨርሰን መስራትና ሰበቡን ጥግ ድረስ ማድረስ ብቻ ነው!!

መንግስት ነባሩን እስልምና ደገፈውም አልደገውም ወላሂ ሱመ ወሊሂ ለመስመሩ አንዳች የሚጨመርለትም ሆነ የሚቀንስበት ነገር የለም!!

መንግስት መስመሩን ቢደገፈው የሚጠቀመው መንግስት ነው! ባይደግፈው የሚጎዳው መንግስት ነው!!

መስመሩ እዚህ ድረስ የደረሰው የማንንም ድጋፍ ሳይሻ ነው!! አላሁ-ታአላ በራሱ መንገድ እንዳመጣው እስከቂያማ ማስቀጠሉ አይቀርም!!

ሌላው ቀርቶ አብይ አህመድ እራሱ ውሃብያ ቢሆን ወላሂ ሱመ ወላሂ ነባሩ እስልምና ላይ ምንም ነገር መፍጠር አይችል!!

ሃረመኒ ሆቴል 400 ኡለሞች ስብሰባ በኋላ ወደ ሳሪስ መስጂድ አቅንተው የዱአ ፕሮግራም ቀጥሏል እዛ የዱአ ፕሮግራም ለከባድ ግዜ የሚቀራ ከሰላሳ አመት በፊት የተዘጋ ኪታብ ነው አንስተው አዋራውን አራግፈው የቀሩት!!

ወላሂ ከዚህ መስመር ጋር ተጋጭቶ የሚዋድና የሚወረድ እንጂ መቆም የሚችል አንዳችም ሃይል አለም ላይ የለም!!

ትላንት እራሳቸውን ከመንግስት በላይ ሲያስቡ የነበሩ ሰዎች ከኛ ጋር ሳይሆን ከመስመሩ ጋር የተጋጩ ቀን ነው መውረድን ወርደው የተዋረዱትና ዛሬ የኛ መቀለጃ ሆነው የቀሩት!!

እኛ እዚህ የምናደርገው ጥቂት እንቅስቀሴ ባጢልን በመጋፈጥና ሃቅን በማንገስ የራሳችንን ጡብ በማኖር የወቅቱ የታሪክ አካል ለመሆን እንጂ እንደ ዉሃበያ/ኢኽዋን ዱኒያዊ አቅምና ሴራ እንደኛ ዱኒያዊ አቅም ማነስና የዋህነት ቢሆን ወላሂ መስመሩንም እኛንም ድሮ አጥፍተውት ተደላድለው በተቀመጡ ነበር!!

ግና መንገዱ የአላህ ነው! የአብይ መንግስትም ሆነ አለም ላይ ያለ የትኛውም ሃይል የፈለገውን ያህል ሴራ ቢሸርብ ወላሂ አላህ በፈለገው መንገድ መስመሩን እስቂያማ ማስቀጠሉ አይቀርም!!

ከኛ የሚጠበቀው መስራት ያለብን ሰርተን ሰበብን ጥግ ማድረስና ተወኩላችንን ሙሉ ለሙሉ አላህ ላይ ማድረግ ነው!ከዛ በተረፈ አላህ የፈለገው ብቻ ነው የሚሆነው!!

Filed in: Amharic