>

የአማራ ሕዝብ ዐብይ ድክመት ! (መስፍን አረጋ)

የአማራ ሕዝብ ዐብይ ድክመት !

መስፍን አረጋ


ጠላቴ ጠፍቶኝ ሳስስ በነፍሴ

ሁኖ አገኘሁት እኔው ራሴ፡፡

የራሴን ጉልበት እንዳልገነባ

ጊዜ ሳጠፋ በረባ አልረባ

በራሴው ድክመት ጠላቴ ገባ፡፡

ጠላት \የሚገባው\ በደካማ ጎን ስለሆነ፣ የሽንፈት ምንጩ የራስ ድክመት እንጅ የጠላት ጥንካሬ አይደለም፡፡  ፈረንጅና ዐረብ ያልደፈረው ታላቁ የአማራ ሕዝብ በመጀመርያ በወያኔ አሁን ደግሞ በኦነግ ይሄን ያህል ሊዋረድ የቻለው በወያኔም ሆነ በኦነግ ጥንካሬ ሳይሆን በሱ በራሱ ድክመት ብቻ ነው፡፡  የአማራን ሕዝብ ለወያኔና ለኦነግ ጥቃት ያጋለጡት ድክመቶች በርካታ ሲሆኑ፣ ከነዚህ ድክመቶች ውስጥ አንዱና ዋናው ደግሞ ዋና ጠላቱን ለይቶ አውቆ በዚሁ ዋና ጠላቱ ላይ ዋና ትኩረቱን አለማድረጉ ነው፡፡   

መለስ ዜናዊ የአማራን ሕዝብ ለሩብ ክፍለዘመን ያህል ሊቀጠቅጥ የቻለው፣ ወያኔን በማጠናከር ሳይሆን አማራን በማዳከም ነበር፡፡  ምክኒያቱ ደግሞ ወያኔ የጠነከረውን ያህል ቢጠነክርም ያልተዳከመን አማራ ሊቀጠቅጥ ቀርቶ ሊቆነጥጥ እንደማይችል በደንብ ስለሚያውቅ ነበር፡፡  ወያኔን ያጠናክሩለት የነበሩትን ወያኔወቹን ኃየሎም አርአያን፣ ሰየ አብርሃን፣ ገብሩ አስራትንና መሰሎቻቸውን ባንድም በሌላም መንገድ አስወግዶ፣ አማራን የሚያዳክሙለትን ብአዴኖቹን አዲሱ ለገሰን፣ ተፈራ ዋልዋን፣ በረከት ስምዖንንና መሰሎቻቸውን ቁልፍ ሰወቹ ያደረጋቸውም ለዚሁ ዓላማው ሲል ብቻ ነበር፡፡

የዘመኑ የአማራ ሕዝብ ዋና ጠላት ደግሞ ሌላ ማንም ሳይሆን የወያኔና የኦነግ ዲቃላ የሆነው ጭራቅ አሕመድ ነው፡፡  ይህ በልቶ የማይጠረቃ ጭራቅ አማራን በልቶ ለመጨረስ ቆርጦ የተነሳው፣ ልክ እንደ አባቱ እንደ መለስ ዜናዊ አማራን በማዳከም ነው፡፡  ለዚህ ምክኒያቱ ደግሞ ኦነጋዊ አራጅ ሠራዊቱን ያጠናከረውን ያህል ቢያጠናክረውም አማራ ካልተዳከመ ግን የአማራን ሕጻናት ሊያርድ ቀርቶ ዝንባቸውን እሽ ሊል እንደማይደፍርና፣ እደፍራለሁ ካለ ደግሞ የሸዋ ፋኖ ብቻ ልክ እንደሚያስገባው ስለሚያውቅ ነው፡፡  ስልጣን ከያዘበት ዕለት ጀምሮ ሙሉ ትኩረቱን ያደረገው አራጅ ሠራዊቱን የሚያጠናክሩለትን ኦነጋውያን በማሰባሰብ ላይ ሳይሆን፣ አማራን ያጠናክሩብኛል ብሎ የሚፈራቸውን ሰወች በመበታተን ላይ የሆነበትም ምክኒያት ይሄውና ይሄው ብቻ ነው፡፡ 

ስለዚህም የአማራ ሕዝብ መዳኛው መንገድ አንድና አንድ ብቻ ነው፡፡  እሱም ተሟሙቶም ቢሆን ጭራቅ አሕመድን በማናቸውም መንገድ ባስቸኳይ ማስወገድ ነው፡፡  መለስ ዜናዊ ሲከፈን፣ ወያኔ እንደ በነነ ሁሉ፣ ጭራቅ አሕመድም ሲወገድ፣ ኦነግም ዐመድ እንደሚሆን ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡  የአማራ ሕዝብ ጭራቅ አሕመድን ባስቸኳይ ጨርቅ ካደረገ፣ ወያኔና ኦነግ እዳቸው ገብስ ነው፡፡   

የአማራ ሕዝብ ሆይ!

ሊገልህ የመጣን ዐልመህ በተለይ

መምታትህን እንጅ ወሳኝ ብልቱ ላይ፣

ጭራሽ አያሳስብህ የመሞቱ ጉዳይ፡፡

በታችም በምድር በላይም በሰማይ

ወንጀለኛ አይደለም አልሞት ባይ ተጋዳይ፡፡

Email:  mesfin.arega@gmail.com

Filed in: Amharic