>

የሰሜኑ ጦርነት እንዲያልቅ አይፈለግም -  የዥዋዥዌ ጨዋታ ነው የያዙት ...! (ግርማ ካሳ)

የሰሜኑ ጦርነት እንዲያልቅ አይፈለግም –  የዥዋዥዌ ጨዋታ ነው የያዙት …!

ግርማ ካሳ


ይሄ ተያዘ:  ያ ተለቀቀ ለሚል ስሜታዊ ፕሮፖጋንዳ ጊዜ የለኝም:: ከዚህ ጋር በተገናኘ የማዘንና   የመደሰት  የዥዋዥዌ ጨዋታ ሰልችቶኛል::

ጥያቄዎቼ  ተያዘ : ተለቀቀ የሚል ጨዋታ መቼ ነው የሚቆመው ? ጦርነቱ በድርድር ይሁን በአንዱ አሸናፊነት መቼ ነው የሚጠናቀቀው ?  ትግራይ: ጎንደር:  ወሎና እፋርም ያለው ህዝብ  መቼ ነው ሰሳም የሚያገኘው ?  የሚሉት ናቸው::

ወገኖች ዋናውና ትልቁ ተጠያቂው የብልፅግና መንግስት ነው::

1ኛ ብዙ ጊዜ በጦርነት ህወሃትን ሙሉ ለሙሉ ማሸነፍ ሲቻል ጫፍ ሲደረስ ተኩስ አቁሙ እያለ ህወሃትን ማዳን ብቻ ሳይሆን እንደገና እንድትጠናከር እድል የሰጠና የሚሰጥ መሆኑ ነው::

2ኛ ህወሃቶች ለድርድር  ፍቃደኛ እንዲሆኑ : ቢያንስ ሁሉንም ባይሆን ግማሽ የጠየቁትን የአብይ መንግስት መሟላት ይችል ነበር:: መብራት: ኔትዎርክ የመሳሰሉት ማስጀመር ችግር  አልነበረም:: ለህዝብ የሚያስብ መንግስት ቢሆን ኖሮ ህወሃቶች ሳይጠይቁ ማድረግ ነበረበት::

እነዚህን መሰረታዊ አገልግሎቶች ማሟላት ቢቻል ኖሮ ምን አልባትም ህወሃት ወደ ውጊያ እንዳትሄ ህዝቡም ጫና ያደርግ  ነበር::  ህወህት ጦርነቱን እንዳያቆም ሰበብ ነው የሰጡት::

ነገር ግን የአብይ መንግስት በሰሜን ሰላም እንዲኖር የሚፈልግ አይመስኝም:: ትግሬውና አማራው እየተገዳደለ : ሰሜኑ በጦርንቱ ምክንያት እየቆረቆዘ: ህዝቡም እየደኸየ : እነርሱ ተረጋግተው በሸገር እየተምነሸነሹ ለመቀጠል ነው የሚፈልጉት::

የሚያሳዝነው ተጋሩዎችም አማራዎችም ይሄን መገንዘብ አለመቻላቸው ነው::ለነ ወልቃይት: ለነ ራያ ቀላል ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርግ  መፍትሄ እያለ: እልህ ስላለ: መነጋገር ሲቻል መተላለቅ አሳዛኝ ነው:: በተለትም ህወሃቶች ጋር ያለው ግትርነት ነው ከአማራው ጋር መነጋገርን አስቸጋሪ ያደረገው::

አሁንም እላለሁ:: የአብይ አህመድ መንግስት በውሸት ላይ የተመሰረተ ነው::  ሆን ብሎ ድርድሩ እንዳይሳካ እንዲጏተት ሊያደርግ ይችላል:: ለምን በሰሜን ሰላም መምጣቱ ለስልጣናችን ያሰጋናል ስልሚሉ::  ነገር ግን ቅንነት በተሞላበት መልኩ ከአማራ ሃይሎች ጋር  በተጏዳኝ መነጋገር ቢጀምሩ የተሻለ ውጤት ሊያመጡ ይችላሉ::

Filed in: Amharic