>
5:13 pm - Wednesday April 19, 3443

ጭራቅ አሕመድ፤ እኩይ አዟሪት የገባ ኦነጋዊ አውሬ! (መስፍን አረጋ) 

ጭራቅ አሕመድ፤ እኩይ አዟሪት የገባ ኦነጋዊ አውሬ!

መስፍን አረጋ 


ያንድ ብሔር አባል አለመሆኑ የሚጠረጠር ግለሰብ የዚያ ብሔር ብሔርተኛ ከሆነ፣  ጥርጣሬውን ለማስወገድ ሲል ብቻ ማናቸውንም አረመኔያዊ ድርጊት ለመፈጸም ቅንጣት አያቅማማም፡፡  ሂትለር ይሁዳወችን ያለ ርኅራኄ የጨፈጨፈበት አንዱ ምክኒያት፣ የይሁዳ ደም አለበት የሚባለውን ጭምጭምታ ለማስተባበል ነበር፡፡  ምሥራቅ አውሮጳውያን (ቸኮች፣ ፖሊሾች፣ ዩክሬኖች፣ ክሮአቶች…) ካንግሎ ሳክሶኖች በከፋ ሁኔታ ዘረኛ መስለው ለመታየት የሚጥሩት፣  ከነጭ አይቆጥሩንም ለሚሏቸው ለምዕራብ አውሮጳውያን ነጮች መሆናቸውን ለማስመስክር ሲሉ ነው፡፡  ያሜሪቃ ጥቁር ፖሊስ ከነጭ ፖሊስ የበለጠ በጥቁር ላይ የሚጨክነው፣ ታማኝነቱን ለነጭ አለቆቹ ለማሳየት ነው፡፡  ባባቱ አማራ ነው የሚባለው ጌታቸው አሰፋ ያማራ ሳጥናኤል የሆነው፣ ትግሬነቱን ለማስመስከር ነበር፡፡  

ጭራቅ አሕመድ ደግሞ በናቱ አማራ ነው ይባላል፡፡  አባቱ ደግሞ ኦሮሞ ናቸው ይባላሉ (ኤርትሬ ናቸው የሚሉም አሉ)፡፡  በዚያ ላይ ደግሞ የተጋባው ከጎንደሬ ጋር ነው፡፡  ስለዚህም በጎጠኝነት የሰከሩት የኦሮሞ ጽንፈኞች ጭራቅ አሕመድን ከአሮሞ አይቆጥሩትም፡፡  እንደማይቆጥሩት ደግሞ እሱ ራሱ በደንብ ማውቅ ብቻ ሳይሆን አልቅጥ ያስጭንቀዋል፡፡  ኦሮሞነቴን ማንም አይሰጠኝም አይነፍገኝም፣ እናቴ አማርኛ አትችልም እያለ ሳይጠይቁት የባጥ የቆጡን የሚቅባጥረው ይሄን ጭንቅቱን ለማለዘብ ነው፡፡

ጭራቅ አሕመድ፣ ፀጋየ አራርሳና የመሳሰሉት ግማሽ አማራ ናቸው የሚባሉ የኦሮሞ ጎጠኞች በኦሮሞነታቸው ስለሚጠረጠሩ፣ ባይነ ቁራኛ እንደሚጠበቁና እያንዳንዷ ድርጊታቸው በጢኖፓይፋ (microscope) እንደምትመረመር አሳምረው ያውቃሉ፡፡  ትንሽ ቢሳሳቱ ግዙፍ ውለታቸው መና ቀርቶ ከሃዲወች እንደሚባሉ ነጋሪ አያስፈልጋቸውም፡፡  እስከጣፈጡ ድረስ ተላምጠው የሚተፉ አገዳወች እንደሆኑ በደንብ ያውቃሉ፡፡  ስለዚህም እነዚህ ግማሽ አማራ ናቸው የሚባሉ ኦነጋውያን ለኦነግ ፀራማራ ዓላማ ሽንጣቸውን ገትረው የቆሙ መሆናቸው ጥርጣሬ ውስጥ እንዳይገባ ሲሉ ብቻ ፣ ማናቸውንም ፀራማራ ድርጊት ለመፈጸም ቅንጣት አያቅማሙም፡፡   ከለማበት የተጋባበት እንዲሉ፡፡

“ግማሽኦሮሞ” ኦንጋውያን “ከሙሉኦሮሞ” ኦነጋውያን እጅግ የከፉ ጽንፈኞች ናቸው፣ መሆንም አለባቸው፣ ግዴታቸው ነውና፡፡  ለምሳሌ ያህል ለማ መገርሳና ጃዋር ሙሐመድ፣ “ሙሉኦሮሞ” ሆኑም አልሆኑም በኦሮሞነታቸው ስለማይጠርጥሩና ኦሮሞነታቸውን የማረጋገጥ ሸክም (burden of proof) ስላልተሸከሙ፣  ጭራቅ አሕመድ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚጭክነውን ያህል እንደማይጭክኑ በርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡  

ጭራቅ አሕመድ እጅግ አረመኔ በላዔ አማራ ጭራቅ መሆኑን በስካሁን ድርጊቱ በግልጽ ያስመሰከረ ቢሆንም፣ ግማሽኦሮሞ ስለሚባል ብቻ ኦነጋውያን መቸም ቢሆን በሙሉ ልብ አያምኑትም፡፡  ስለዚህም ኦነጋውያን ትናንት ከሚያምኑት የበለጠ ዛሬ እንዲያምኑት ከፈለገ ትናንት ካደረገው የከፋ ዛሬ ማድረግ አለበት፡፡    ስለዚህም የአማራን ሕዝብ በተመለከተ ጭራቅ አሕመድ የበለጠና የበለጠ ጭራቅ እየሆነ ይሄዳል፣ መሄድም አለበት፡፡  

ጭራቅ አሕመድ በአማራ ሕዝብ ላይ ነገ የሚያደርገው ትናንት ካደረገው የክፋ እንደሚሆን ከስካሁን ድርጊቱ በመነሳት ብቻ በርግጥኝነት መናገር ይቻላል፡፡  ትናንት በሺወች አርዷል፣ ነገ ባስር ሺወች፣ ከነግ ወዲያ ደግሞ በመቶ ሺወች ያርዳል፡፡  ለዚህ ደግሞ በስልጣኔ ብትመጡብኝ መቶ ሺወች ባንድ ጀምበር ይታረዳሉ በማለት እሱ ራሱ፣ በራሱ አንደበት የተናገረውን መጥቀስ ብቻ ይበቃል፡፡  ትናንት ቶሌ ላይ ያማራን ሕጻናት ግዳይ ጥሏል፣ ነገ ጉለሌ ላይ፣ ከነገ ወዲያ ደግሞ ቦሌ ላይ ግዳይ ይጥላል፣ እሱ ራሱ ዛሬውኑ ካልተጣለ በስተቀር፡፡   

ባጭሩ ለመናገር ጭራቅ አሕመድ በማንነቱ ምክኒያት መቸም ከማይወጣበት እኩይ አዟሪት (vicious circle) ውስጥ የገባ ኦነጋዊ አውሬ ነው፡፡  ካዟሪቱ የሚያወጣው ደግሞ ሞቱ ብቻ ነው፡፡  የአማራ ሕዝብ መዳን የሚችለው ደግሞ ጭራቅ አሕመድን በማናችውም መንገድ ጨርቅ በማድርግ ብቻና ብቻ ነው፡፡  የአማራ ሕዝብ ጭራቅ አሕመድን ጨርቅ ካደረገ፣ ወያኔና ኦነግ እዳቸው ገብስ ነው፡፡  ያሳ ግማቱ ካናቱ ነውና፣ አማራ ሆይ ሙሉ ትኩረትህን አራት ኪሎ ላይ አድርገህ፣ በማናቸውም መላ የግሙን አናት ቅላ፡፡ 

 Email: mesfin.arega@gmail.com

Filed in: Amharic