>

በአለም የተካሄዱ የዘር ማጥፋት ወንጀሎችና  የኦሮሙማው የአፓርታይድ  የሚያካሄደው የዘር ማጥፋትና የጅምላ ፍጅት! (አቻምየለህ ታምሩ)

በአለም የተካሄዱ የዘር ማጥፋት ወንጀሎችና  የኦሮሙማው የአፓርታይድ  የሚያካሄደው የዘር ማጥፋትና የጅምላ ፍጅት!  

አቻምየለህ ታምሩ


የዘረኝነት ፖለቲካን ርዕዮተ ዓለሙ አድርጎ በመንግሥትነት የተሰየመ ቡድን የሕዝብ እልቂት ሳያስከትል የተወገደበት የታሪክ አጋጣሚ የለም። ኦሮሚያ ተብሎ በሚጠራው የገሀነም ምድር በዐቢይ አሕመድ በሚመራው የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝ እየተፈጸመ የሚገኘው አገዛዝ መር የጅምላ ፍጅት፣ የንጹሐን እልቂት፣ የዘር ማጥፋትና የጦር ወንጀል በሁቱ ኢንተርሃሞዮች ስር ከነበረችው ሩዋንዳና በናዚዎች ቁጥጥር ስር ከነበረችው ጀርመን ጋር ተመሳሳይ ነው። ከአቅም ውስንነት በስተቀር በኦሮሙማው የጽልመት የኃይልና በሁቱዎቹ የኢንተርሃሞይና በናዚዎቹ የዌርማክት ኃይሎች መካከል የአላማ ልዩነት የለም።

ኢንተርሃሞይና ዌርማክት አለምን የዘገነነውን የዘር ማጥፋትና የጅምላ እልቂት ያካሄዱት የባንኩም የታንኩም ጌቶች እንዲሆኑ ያስቻላቸውን የመንግሥትነት ስልጣን በመቆጣጠራቸው ነው። በዐቢይ አሕመድ የሚመራው አውዳሚው ኦሮሙማም ባለፉት አራት ዓመታት የአገሪቱን ካዝና ያለከልካይ በመቆጣጠሩ በየጫካውና ከተማው የዘር ማጥፋትና የጅምላ እልቂትን ያለ ማንም ከልካይ ለማካሄድ የሚችልበትን አቅም ፈጥሯል። ከዚህ በተጨማሪ የኦሮሞ ብሔርተኞች ኹሉ ያለ ልዩነት በኦሮሙማው የአፓርታይድ አገዛዝና ቅርንጫፎቹ እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጥፋትና የጅምላ ፍጅት ደጋፊዎች ናቸው።

በሌላ አነጋገር በሩዋንዳና በጀርመን የተካሄደው አይነት የዘር ማጥፋት በዚህ ዘመን በኢትዮጵያ ምድር እየተካሄደ ያለው በስልጣን ላይ ባለው በዐቢይ አሕመድ በሚመራው የኦሮሙማው አፓርታይዳዊ አገዛዝ ብቻ ሳይኾን የአገዛዙ አላማ ተጋሪ በሆኑ የኦሮሞ ብሔርተኞችና የፖለቲካ ደጋፊዎቻቸውና የታጠቁ ሚሊሻዎች ጭምር ነው።

ኦሮምያ የሚባለው የንጹሐን መታረጃ ቄራ የምድር ሲዖል እስኪመስል የአማራ ተወላጆችና ኢትዮጵያን ይወድዳሉ የሚባሉት ኹሉ በተገኙበት ቦታ ሁሉ እንደ እንስሳ እየታደኑ በግፍ እንዲጨፈጨፉ አመራር በመስጠት በዓለም አሰቃቂ ወንጀል እንዲፈፀም አመራር የሚሰጠውና የሚያቀነባብረው በዐቢይ አሕመድ የሚመራው የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝ ቢሆንም በፋሽስት ወያኔ ዘመን ገርበብ ብሎ ተከፍቶ የነበረው የሲኦል በር በኦሮሙማ አፓርታይዳዊ አገዛዝ በጥንቱ ቢዛሞ በጽልመት ስሙ ወለጋ እየተባለ በሚታወቀው የግፉአን መቃብር  ተበርግዶ የተከፈተው የምድር ሲዖል የኦሮሞ ብሔርተኞች ሁሉ ጉባዔ አድርገው “ጋዲሳ ሆግንሰ ኦሮሞ” የሚል ማኅበር በመመስረት የአማራ ነገድ አባላትን ለመፍጀት የሚያስችላቸውን የጋራ እቅድ ከተነደፉ በኋላ ነው። በዚህ ጉባዔያቸው መረራ ጉዲና የተናገረውን የጉባዔው ተሳታፊ የነበረ ፓስተር ነግሮናል።

የኦሮሙማው አረመኔያዊ አገዛዝና ተከታዮቹ በ“ጋዲሳ ሆግንሰ ኦሮሞ” ተወስኖ በወለጋ በርግደው የከፈቱትን የሲዖል በር አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎችም በርግደው ለመክፈት ስራቸውን አጠናቅቀው ወቅትና ሁኔታ እየተጠባበቁ ነው። አዲስ አበባ ውስጥ ለመፈጽም ያሰቡትን ከወዲሁ ጀምረውታል።

የሲዖል በሩ በቅድሚያ ተበርግዶ የሚከፈተው በአማራ፣ ኦሮሞ አይደሉም በተባሉና ኢትዮጵያ ወዳድ ናቸው ተብለው በሚለዩ  ኦሮሞዎችና የኦሮሙማን ውድመት በማይቀበሉ ሙስሊምና የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ሁሉ ላይ ነው። የጦር ኃይሉንና ሌሎች የጸጥታ አካላት ቁልፍ ቦታዎች በኦሮሙማ ጉዳይ አስፈጻሚ የኦሮሞ ብሔርተኞች የተያዘ በመሆኑ ተበርግዶ የሚከፈተውን የሲኦል በር ገርበብ ለማድረግ የሚያስችል መንግሥታዊ ኃይል አይኖርም።

የዘር ማጥፋትና  የባህል ድምሰሳ በመካከለኛ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያ በኦሮሞ አባገዳዎች፣ በላቲን አሜሪካና አውስትራሊያ ደግሞ በነጮች በተሳካ ሁኔታ ተፈጽሟል። እነዚህ የዘር ማጥፋትና የባህል ድምሰሳ ወንጀሎች በተሳካ ሁኔታ ሊካሄዱ የቻሉት ግን በዚህ ዘመን እንደሚፈጸሙ የወንጀል ተግባሮች በአጭር ጊዜ ዘመቻ ሳይሆን መቶና ሁለት መቶ ዓመት በመፍጀት ነው።

ከሀያኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወዲህ የተካሄዱ የዘር ማጥፋት ዘመቻዎች ደፍጥጦ በሚያነደድ ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የተካሄዱ  ሲሆኑ የብዙ ሰው ሕይወት የማጥፋት ችሎታ ቢኖራቸውም ከአጭር ጊዜ የፖለቲካ ስሌት ውጭ በአብዛኛው ተሳክተው አያውቁም። እንዴውም በዘመናዊው አለም የተሞከሩ የዘር ማጥፋት ዘመቻዎች ባርቀው ወንጀለኞች ካሰቡት በተቃራኒው የተለየ ውጤት አስከትለው አልፈዋል።

በጀርመንየ ናዚ ጽንፈኞች ቁጥራቸው ወደ ስድስት ሚሊዮን የሚጠጋ አይሁዳውያንን ለማጥፋት ያካሄዱት የዘር ማጥፋት ዘመቻ በዓለም ላይ ኃያል የሆነ የአይሁድ ሕዝብን ፈጠረ እንጂ አላጠፋቸውም። በአንጻሩ የጀርመንን ሕዝብ ለዘመናት እየተሸማቀቀ አንዲኖር አድርጓል። የአገሪቱ 85% የሆነውን የሁቱን ሕዝብ እንወክላለን ብለው የተነሱት የሩዋንዳ ጽንፈኞች የጀመሩት ቱትሲዎችን የማጥፋት ዘመቻ ከሽፎ ሁቱዎች በገዛ አገራቸው ሁለተኛ ደረጃ ዜጋ ሆነው እንዲኖሩ አደረገ እንጂ አልተሳካም። ዘር አጥፊዎችና ተከታዮቻቸው የነበሩ ጽንፈኞች እጣ ፈንታም በመላው ዓለም ከየተደበቁበት እየተለቀሙ መታደን ነው የሆነው።

ናዚን የወለደው ፕሮጀክት ፍጥረት የሆነው ኦሮሙማ ዛሬ ጽንፈኞቹ  እያካሄዱት ያለው የዘር ማጥፋትና የጅምላ እልቂት ውጤቱ የመንፈስ አባቶቻቸው በሆኑት ናዚዎችና ኢንተርሐሞዮች ላይ ከደረሰው የተለየ ሊሆን አይችልም። የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝና ደቂቆቹ በመንግሥትነት ተሰይመው የታንኩና የባንኩ የበላይ ስለሆኑ ዘግናኝ  የዘር ማጥፋት፣ የጅምላ ፍጅትና እልቂት መፈጽም የሚችሉበትን አቅም ቢፈጥሩና ከጽንስ እስከ አዛውንት ንጹሐንን ቢፈጁም የሚፈጽሙት ይርጋ የሌለው ወንጀላቸው ግን ፍጻሜያቸውን  በመላው አለም እየታደኑ ለፍርድ ከቀረቡት የመንፈስ አባቶቻቸው ከሆኑት ናዚዎች የተለየ አያደርገውም።

በርግጥ የኦሮሙማው የዘር ፍጅትና የጅምላ ጥፋት ከሩዋንዳና ከጀርመን ናዚ ጥፋት የሚለይበት የታሪክ ዳራ አለው። ከዘጠና በመቶ  በላይ የሚሆነው ኦሮምኛ ተናጋሪ የሆነው ሕዝብ ማንነቱን በኃይል የተቀማና በግድ ኦሮሞ የተደረገ የአባገዳዎች ገርባ ወይም ባርያ ነው። ከዚህ በተጨማሪ ኦሮሚያ በሚል ጀርመኖች ባወጡት ስም የተሰየመው የኢትዮጵያ መሬት እንደ ሕዝቡ ሁሉ በወረራና በዝርፊያ የተካለለ ጥንተ ባለቤት ያለው የነባር የኢትዮጵያ ነገዶች አጽመ ርስት ነው።

እነዚህ የታሪክ ዳራዎች በጀርመንና ሩዋንዳ ጽንፈኞች ካካሄዷቸው የዘር ማጥፋት ዘመቻዎች  ኦሮሙማ በኢትዮጵያ የሚያካሂደውን  የዘር ጅፍት፣ የጅምላ እልቂትና ዘግናኝ ጭፍጨፋ  ልዩ ያደርጉታል። ሩዋንዳና ጀርመን ውስጥ የዘር ማጥፋቱን ዘመቻ ያደረጉት ጽንፈኞች አብላጫ ቁጥር ከነበረው ማኅበረሰብ የወጡ ናቸው። የዘር ማጥፋት ዘመቻው የተደረገው በቁጥር በጣም አነስተኛ በሆነው ማኅበረሰብ ላይ ነው።

ባጭሩ የዘር ማጥፋት ዘመቻ አጸፋው በአጥፊዎች ላይ የከፋ ነው።  የዘር ማጥፋት ጦርነት የተደረገባቸው ሕዝቦች በመጨረሻ ነጻ ሲወጡ በሰላም የመኖር ዋስትናቸውን ለማስጠበቅ የተለያዩ ሕጎችና ሥርዓቶችን ፈጥረዋል። ለምሳሌ በሩዋንዳ ውስጥ 85% ሕዝብ ምንም እንኳን ሁቱዎች ቢሆኑ ላለፉት 30 ዓመታት ግን በተግባር  ያለምንም መብት ሁለተኛ ደረጃ ዜጋ ሆነው እንዲኖሩ ተገደዋል።

የጀርመንና የጃፓን ሕዝብና መንግሥት የናዚዎች የብሔረተኝነት ምልክቶችን ማሳየት፣ ማሞገስ፣ ወንጀል አድርገው፣ እንደ ሕዝብ በሄዱበት ሁሉ በቀልድም፣ በቁም ነገርም እየተነሳ ተሸማቀው ለመኖር ተገድደዋል። ይህ ብቻ አይደለም፣ አንዳንድ አይነት የጦር መሳሪያዎችን እንዳይዙ፣ የወታደር ቁጥራቸውን ከተወሰነ በላይ አንዳይሆን፣ አገር ቢኖርቸውም ግን ነጻነታቸውን ተገፈው እስካሁን አሉ። ጀርመናዊ ጀርመናውነቱን፣ ጃፓናዊ ጃፓናውነቱን በግልም ሆነ በሕዝብ ደረጃ መፋቅ ስለማይችሉ ይህንን አሸማቃቂ ሁኔታ ተቀብለው ለመኖር ተገደዋል።

አረመኔያዊው ኦሮሙማም ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር እያደረገ ያለው የጅምላ እልቂትና የዘር ማጥፋት በአጥፊዎቹ ታድነው ለፍርድ ከመቅረባቸው ባሻገር ማንነቱ ተነጥቆ በግድ ኦሮሞ ነህ የተባለው ሕዝብና ከአጽመ ርስቱ የተነቀለው ሕዝብ የተቀማውን ማንነትና የተነጠቀውን አጽመ ርስቱን ለማስመለስ እንዲሁም ኦሮሙማ ካደረሰበት ሁለንተናዊ የታሪክ ጠባሳ የሚፈወስበትን ጎህ እንዲቀድድ ያደርገዋል። ይህም በሌሎቹ አገሮች የዘር ማጥፋት ከተፈጸመ ከብዙ አስርተ ዓመታት በኋላም ሳይጠፋ የቆየው ፍርሃትና ጥላቻ በኢትዮጵያ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል ያደርገዋል። በወራሪ አባገዳዎች በኃይል ማንነቱን እንዲቀይር የተደረገው ሕዝብ ቁጥር አሁን ካለው ቢያንስ በ90% ስለሚቀንስ ዘር አጥፊውና አውዳሚው ኦሮሙማ በሌላ ዙር የሚያስነሳው ጽንፈንነት የሚማግደው ነዳጅ አያገኝም። ይህ የኦሮሙማ ቅዠት ተፈጥሯዊ ሞቱን እንዲያሸልብ ያደርገዋል።

ኦሮሙማ በርግዶ የከፈተው ቤርሙዳ የበላውን በልቶ በሕዝባዊ ተጋድሎ እስኪወገድ ድረስ እያንዳንዱ ዜጋ የራሱን፣ የቤተሰቡንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ለማትረፍ አቅድ አውጥቶ መስራት ግድ ይለዋል። ራስን ከመከላከል ጀምሮ ሕይወት የሚተርፍበትና የተጎዱ የሚረዱበትን መንገድ እያንዳንዱ ሰው መተለም ይኖርበታል። መተባበር የግድ ቢሆንም፣ በኦሮሙማው የአፓርታይድ አገዛዝ እየተፈጸመ የሚገኘውን የዘር ማጥፋት፣ የጅምላ እልቂትና ዘግናኝ ጭፍጨፋ ለመቋቋም በአንድ ማዕከል በሚካሄድ ተጋድሎ፣ በአንድ መሪ በሚሰጥ ስምሪት መጋፈጥ ይቻላል ተብሎ የሚገመት ነገር አይደለም። ታንክና ባንክ የተቆጣጠረው የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝ የሚያካሂደውን የዘር ፍጅት መግታት የሚቻለው ሁሉም ባለበት ቦታና ሰዓት ራሱን ከአላማ ተጋሪዎቹ ጋር አደራጅቶ በሚያደርገው ተጋድሎ ነው።

ከዚህ በተጨማሪ የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝ  እያደረሰ ያለውን የሰቆቃ ጊዜ በተሳካ ሁኔታ ማለፍ የሚቻለው ኢትዮጵያዊ አቃፊነትን ከምንም ጊዜ በላይ ከፍ በማድረግ፣ ታሪክን በትክክል በመገንዘብ፣ ፍትሕን በትክክል በማዳረስና በቀልን በማስወገድ ጭምር ነው።

የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝ እያደረሰው ያለው አይነት የጅምላ እልቂት፣ የዘር ማጥፋትና ውድመት በኢትዮጵያውያን ላይ ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ በዚህ ምድር ላይ እስካለ ድረስ እንዳይደገም ማድረግ የሚቻለው የራስን አዎንታዊ አሻራ ለማኖር አሉታዊ ስሜትን መግታት ሲቻል ነው።

ይህ ጽሑፍ ጥላቻን ለማስፋት የተጻፈ አይደለም። ጥላቻ የተስፋ መቁረጥ፣ የወደፊት ሕይወት ጨለማ ሆኖ የመታየት ውጤት ነው። በመላው ኢትዮጵያና በተለይ በአማራው ማኅበረሰብ ዘንድ በዐቢይ አሕመድ የሚመራው የኦሮሙማ አፓርታይዳዊ አገዛዝ እያካሄደ ባለው የአማራ የጅምላ ፍጅት፣ እልቂትና የዘር ማጥፋት ተደምሬያለሁ ሲል በነበረው ዘንድ ሳይቀር ከፍተኛ  የሆነ ተስፋ መቁረጥ ይስተዋላል። በመንግሥትነት የተሰየሙት የኦሮሙማ ናዚዎች የሩዋንዳ ሁቱ ኢንተርሀሞዮች ያደረሱት እልቂት ቅጂ በአማራ ሕዝብ ላይ እያካሄዱና ሰማዩንም ምድሩንም የነሱ ሊያደርጉ ድኀውን እያፈናቀሉ ያገኙትን ሁሉ ሲሰለቅጡ እያየ አሁንም ተስፋ ቢያደርግ ነበር የሚያስገርመው።

ሆኖም ግን የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝ እያደረሰው ባለው የዘር ፍጅትና የጅምላ እልቂት ተስፋ መቁረጥ እጅና እግር አጣጥፎ ለመቀመጥ ሳይኾን ተደራጅቶ ራስን ወደ መከላከል ደመነፍሳዊ ተጋድሎ ለመግባት መሆን አለበት። ተስፋ መቁረጥ ብቻውን  የሚመጣውን አደጋ አያስቆምም፤ አደጋውን በብዙ እጥፍ አጥፊ ያደርገዋል፤ አደጋ ከደረሰ በኋላ የማገገምያ ጊዜውን ያርቃል እንጂ።

የዚህ ጽሑፍ አላማ ስለወደፊቱ ተስፋ መቁረጥ እጅና እግር አጣጥፎ ለመቀመጥ ሳይሆን በአማራ ሕዝብ ላይ መንግሥታዊ የዘር ፍጅና የጅምላ እልቂት እያካሄደ ያለውን የኦሮሙማ አፓርታይድ አገዛዝ ለመጋፈጥ ተደራጅቶ ራስን ወደ መከላከል ደመነፍሳዊ ተጋድሎ ገፍትሮ በማስገባት ከዋሻው ጫፍ ያለውን ብርሀን ማየት እንደሚቻል ለማሳየት ነው። የኦሮሙማ አፓርታይዳዊ አገዛዝ እያካሄደ ያለውን የአማራ የጅምላ ፍጅት፣ እልቂትና የዘር ማጥፋት እንደማንኛውም ወረርሽኝና ቸነፈር ቆጥሮ በተቻለ መጠን የሚጎዳውን ሕዝብ እንዳይበዛ ለማድረግ መሞከርና ወረርሽኞች ሁሉ እንደሚያልፉ የኦሮሙማው ቸነፈርም እንደሚያልፍ አውቆ ወደ ሰላሙ ጊዜ ለመሻገር ብቸኛው አማራጭ ደም የሚያስተፋ ቁጣ በማሰማት የቸነፈሩን እድሜ ለማሳጠር መነሳት የግድ እንደሚል ለመጠቆም ነው።

በዐቢይ አሕመድ የሚመራው አረመኔያዊ የአፓርታይድ አገዛዝ ሳይወገድ በኢትዮጵያ ምድር በአማራ ሕዝብና ኦሮሞ አይደላችኹም ወይም ኦሮሞ አትመስሉም በተባሉ ኢትዮጵያውያን ላይ እየተካሄደ ያለው የዘር ማጥፋትና የጅምላ ፍጅት ሊቆም አይችልም።  የተቀረው አለም ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ በየዕለቱ እስከ አስር ሺሕ የሚደርሱ ቱትሲዎችና ለዘብተኛ ሁቱዎች ለሶስት ወራት የተጨፈጨፉበት የሩዋንዳ መንግሥት መር የዘር ማጥፋት  መቋጫ ያገኘው በወቅቱ የ36 አመት ጎልማሳ በነበሩት ስደተኛ ፖል ካጋሜ የሚመራው የርዋንዳ አርበኞች ግንባር ሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት አሸንፎ አገሪቱን በቁጥጥር ሥር ሲያውል ነበር። በአገራችንም በዐቢይ አሕመድ በሚመራው ደመኛ የኦሮሙማ አገዛዝ የሚካሄደውን የዘር ማጥፋትና የጅምላ ፍጅት ማስቆም የሚቻለው ግፉአን በሚያደርጉት ተጋድሎ ደመኛውን አገዛዝ አስወግደው አገራቸውን በቁጥጥር ስር ሲያውሉ ብቻ ነው።

Filed in: Amharic