>

"ከገደልኩዋቸው ሰዎች ሁሉ የሙዚቃው ንጉሥ ቦብ ማሪሊ የተለየ ፍጡር ነው" (Bill Oxley የአሜሪካ ስለላ ድርጅት አባል)

 79 ዓመቱ አዛውንት የአሜሪካ ስለላ ድርጅትን ለ 29 ዓመታት ያገለገለው ” Bill Oxley ” የተባለ የስለላ ድርጅት አባሉ በጤና ቀውስ በሆስፒታል ሳምንት ዕድሜ ብቻ አለህ የተባለው ግለሰብ ቦብ ማሪን መግደሉን ተናዘዘ!
ይህ ግለሰብ የስለላ ድርጅቱን 29 ዓመት በአሳሽ ገዳይነት ባገለገለበት ወቅት በመጨረሻዎች ሃያ ዓመታት ብቻ 17 ግለሰቦችን በታዘዘው መሠረት መግደሉንም አረጋገጠ!!

ለእነዚህ የግዲያ እርምጃ ትዕዛዝ ተቀብሎ ግዳጅን በመቀበል ግዴታውን ለመወጣት መግደሉን እንጂ ግለሰቦቹ ስለሚገደሉበት ምክንያት ለማወቅ ደንታም አልነበረኝም አለ! ሆኖም በአብዛኛው የአሜሪካንን ደህንነት ስጋት ውስጥ የከተቱ ሰዎች እንደሆኑ ብቻ ነው ግንዛቤ ያለኝ ብሏል ፤
ከነዚህ የግድያ እርምጃ ከወሰድኩባቸው ሰዎች እጅግ ልቤን የነካኝና የዘወትር የህይወቴ ዘመን ፀፀት የሆነብኝ የ 36 ዓመቱ ለግላጋ ወጣትና የራፕ ሙዚቃ አቀንቃኙ ቦብ ማሪሊይ ብቻ ነው ብሏል!
በዚህም ይንን እጅግ ህዝብን ያተራምስ የነበረውን ሙዚቃውን በሰማሁበት ጊዜ ሁሉ በዓይነ ሂልናዬ ውስጥ እየመጣ ሲረብሸኝ ነበር የኖርኩት ስል ይፀፀታል፤
ቦብ ማሪሊን የአሜሪካንን ህልውና የሚፈታተኑ ሙዚቃዎች በመጫወት ከጥይትም ይሁን በቦምብ ጥቃት በላቀ በሙዚቃው እልፍ አዕላፍ ደጋፊዎቹን ሁሉ ያንቀሳቅስ ነበር ብሏል! አልፎም በበርካታ የአለም አገሮችን ፀረ አሜሪካ ተግባራት ውስጥ በሙዚቃው ውስጥ እያጣቀሰ ወጣቱን ያነሳሳው ነበር ብሏል፤
ቦብ ማሪሊንን ኒዬርክ ከቤቱ ሲወጣ በድብቅ ቦታ ጠብቀን በሦስት ጥይት መትተነው ነበር ፣ ነገር ግን ትከሻውንና ክንድን ተጎድቶ ከዚህም ተርፎ ሆስፒታል በመግባት አገግሞ ወደ አገሩ በመመለስ በአንድ ተራራማ ሥፍራ ቤቱ መኖር ጀመሮ ነበር ነበር አለ ገዳዬ!!
በመቀጠልም በአንድ ወቅት የሚኖርበትን ሥፍራ በጥንቃቄ በማጣራት የኒዬርክ ጋዜጣ ፎቶ ግራፍ አንሺ ነኝ በማለት መታወቂያና በአንገቴም የጋዜጤኛ መለያ በማንጠልጠል ካሜራዬን በመሸገም ቤቱ ሄጄ አገኘሁት በማለት በዚህንም ወቅት መጠነኛ ስጦታም በማበርከት ቅርበቱን ካመቻቸሁኝ በኃላ አንድ በርሱ ቁጥር የገዛሁትን ጫማም አበረከትኩለት ይላል ገዳዩ ፣
ይህንን ጫማ ሲሰጠው ጫማውን ሲሞክረው የግራ እግሩን እንዳስገባ በመጠኑ አንድ ነገር ወግቶት ሲያስደነግጠው አይ ነበር ብሏል የስለላ ድርጅቱ መልዕክተኛ፤
ጫማው ውስጥ ትንሽ የካንሰር በሽታን የተሸከመች ደቃቅ መርፌ እግሩን እንድትወጋው በማድረግ ለሞት አመቻችቼው ተለየሁት ቡማለት ይቀጥልና በኃላም የካንሰር ታማሚ በመሆን ፈረንሳይ ሃገርና አሜሪካም መጥቶ ሆስፒታል ተኝቶ ከደዌው ፈፅሞ ማገገም አልቻለም ነበር ! በኃላም እጅግ ከስቶና ሰውነቱ ሁሉ አልቆ ፎቶውን በመጨረሻዎቹ ጊዜ አይቼ ውስጤን እጅግ ረብሾኝ ነበር ብሏል ገዳዩ፤
በመጨረሻም ማያሚ ፍሎርዳ እንደሄደ እዚያው ነው ህይወቱ ያለፈው በማለት ከገደላቸው ሰዎች ሁሉ ማንም ያዘንኩለት የለም ነገር ግን ዘንካታውና ለግላጋው ወጣት የሙዚቃው ንጉሥ ቦብ ማሪሊ ግን የተለየ ፍጡር ነው በማለይ ይህ በጠና እርሱም በመታመሙ ሳምንት ቀረህ የተባለው አሜሪካዊውና የስለላ ድርጅቱ ጡርተኛና የ 79 ዓመት አዛውንት አሜሪካ ማሳቹተስ ስቴት ህክምና ላይ ካለበት ሆስፒታል ይህንን በመናዘዝ ተሰምቶ የማያውቀውን ሚስጢር አጋለጠ ።
Filed in: Amharic