የኔታ ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም !
በጀግኖቻችንን ቤት በመገኘት እንኳን ከእስር ተፈታችሁ በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አሰተላልፈዋል። እጅግ በጣም ትሁት የሆነው ፤ እውቁ ፓለቲከኛ አንዱዓለም አራጌ ፣ እንዲሁም አለም አቅፍ ታዋቂ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ፤ ከእስር መፈታታቸው አስመልክቶ በመኖሪያ ቤታቸው በመገኘት እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ፤ በነበራቸው አጭር ቆይታ እጅግ በጣም ሚዛን የሚደፋ ሃሳቦችን አንስተው ተነጋግረዋል። በስተመጨረሻ ጀግኖች አባቶቻችን እና እናቶቻችን መሰዋዕትነት የከፈሉበት የእናት ሃገር ኢትዮጵያ መለያ ባንዲራ በክብር ለጀግኖቻችን በአደራ ሰጥቷል።
—
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !!