ስለህወሓት ጁንታ፣ ስለኦነግ ሸኔ እና መሰል ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተናገሩት‼
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
የህወሓት አመራሮችን፣ የማዕከላዊ ኮሚቴውን ሁሉ እባካችሁ ብዬ ለምኛለሁ፤ አስለምኛለሁ፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ዋና ዋና ባለሃብቶችን ታዋቂ ግለሰቦችን አሰባስቤ በሚስጥር ልኬ እባካችሁ ለምኗቸው ብዬ ሽምግልናም ልኬያለሁ፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
እብሪት ከፉ ነው፤ አሁንም ያላችሁ አመራሮች ከእብሪት ልትቆጠቡ ይገባል፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
በህግ ማስከበሩ ከ300 በላይ የኦነግ ሸኔ ሽፍታ አብሮ ሲዋጋ ይዘናል፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ኦነግ ሸኔ ለማንም አይበጅም፣ ለሰው ዘር አይበጅም፤ ለኢትዮጵያም ጠላት ነው፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ወለጋ ህዝብ ስቃይ ውስጥ በነበረበት አንድም ሰው አልተናገረለትም፤ ከውጭም ከውስጥም፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ኦነግ ሸኔ በሰላም ተወዳደር ሲባል እንቢ ብሎ የህውሓት ቡችላ ሆኖ ነው አርሶ አደር ገድሎ ሲፎክር የነበረው፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ወለጋ ውስጥ የሞቱት አማራ አርሶ አደሮች አማሮች አይደሉም፤ የኦሮሞ አካል ናቸው፣ እነሱን መግደል ኦሮሞን መግደል ነው፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
በትግራይ ውስጥ ሰዎችን ማፈን አለ፤ ሌለው ቀርቶ እርዳታ የሚሰጡ ሰዎች ይታፈናሉ፣ ይገደላሉ፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
እርዳታ እንዳይሰጡ ተደርጓል፤ በትግራይ ብዙዎች የደረሰውን በደል እያወቁም ሊክዱ ፈልጋሉ፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
በአንድ ቀን በ200 ቦታዎች ላይ ነው በተጠና መልኩ በተመሳሳይ ሰአት ጁንታው ጥቃት የፈጸመው፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ኦነግ ሸኔ የኢትዮጵያ ጠላት ነው፤ ለኦሮሞ አይበጅ፤ ለአማራ አይበጅ ለማንም አይበጅም
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ትግራይ ውስጥ አሁን ሰው ይታፈናል፤ ርዳታ የሚሰጡ ሰዎች ሳይቀር እየታፈኑ ነው፤ ከዚህ ቀደም ካደረጉት ጥፋት በላይ አሁን የሚያደርጉት ይብሳል፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ጁንታው ያኔ 200 ቦታዎች ላይ በተመሳሳይ ሰአት አንድ ላይ ነው ጥቃት የፈጸመው፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
አማራ ክልል ላይ ጥቃት የፈጸመው ይሄው ሃይል ነው፤ ዓላማውም ጎትቶ ወደ ግጭቱ ማስገባት ነው፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ኤርትራ ላይ የተኮሰው ይሄው ሃይል ነው፤ ችገሩን ቀጣናዊ ለማድረግ አስቦ ነው፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
በትግራይ ከ30 ሺህ በላይ እስረኛ ተለቋል፤ መቀሌ ብቻ 10 ሺህ እስረኛ ተለቆ ዝርፊያ ፈጽሟል፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ለትግራይ ህዝብ ጦርነት ግጭት አይገባውም፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
የእኛ የህግ ማስከበር ሶስት ግልጽ አላማዎች አሉት
– በዘሩ ብቻ በማንነቱ ብቻ ለይተው መከላከያ ሰራዊትን የጨፈጨፉትን ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ ነው፤
– ኢትዮጵያን አምነው ለ20 አመት በክልሉ የኖሩ ታግተው የተወሰዱ ከ1000 ሺህ ባለይ መኮንኖችን ማስፈታት ነው፤ መቶ በመቶ አስፈትተናል፤ የገደሏቸውን ቀብረናል፤ የተዘረፍነውን አስመልሰናል፤
– ይህ ክልል ወደ ምርጫ ሄዶ ራሱን እንዲያስተዳድር ነው፤ አሁን ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ በጊዜያዊ አስተዳደር ራሱን እያስተዳደረ
ነው፤ ሊታገዝ ይገባዋል፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
የተበተነው ርዝራዥ ሃይል በየቦታው እየሆነ በመከላከያ ላይ እየተኮሱ ሽንቆጣ ፈጽመዋል፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ማለት ነው፤ ከዚህ በኋላ ተሰብስቦ ዱቄት አይሆንም፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባል ሆኖ በትግራይ ክልል ወንጀል የፈጸመ ካለ በህግ ይጠየቃል፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
በትግራይ ክልል ስለተፈጸመ ችግር የሚያነሱ በሰሜን ዕዝ ላይ ስለተፈጸመው ግፍ አያነሱም፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
በማይካድራ ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ በኢትዮጵያ ውስጥ በየትኛውም አካባቢ አልተፈጸመም፤ ግን ተረስቷል፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
ቤንሻንጉል ላይ ስላለው ጭፈጨፋ ማንም አይናገርም፤ ትኩረት ሁሉ አንድ አካባቢ የሆነው የተንሸዋረረ እይታ ስላለ ነው፤
![👉](https://mail.google.com/mail/e/1f449)
በትግራይ ከተካሄደው ኦፕሬሽን በኋላ 4.2 ሚሊዮን ህዝብ መግበናል፤
ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን።