>
5:13 pm - Wednesday April 20, 7701

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተናገሩት‼

“ባለፉት ሳምንታት በሰሜን ሸዋ እና በጎጃም ያያችሁት ዝናብ የተፈጥሮ ሳይሆን እኛ ያዘነብነው ነው”
 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተናገሩት‼
*..  ስለህወሓት ጁንታ፣ ስለኦነግ ሸኔ እና መሰል ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ  የተናገሩት‼
 
*… የአማራ ልዩ ሀይልን በሚመለከት የተናገሩት
 
👉 ዓለም ላይ ያላቸውን ደመናን ወደዝናብ የቀየሩ አገራት ጥቂት አገራት ናቸው፤
👉 እኔ ኢትዮጵያ ውስጥ መቼ አየዋለሁ ብዬ ከምቀናባቸው ነገሮች አንዱ ይሄ የተከማቸ ደመና በተመረጠ ሁኔታ ማዝናብ መቻልን ነው፤
👉 አሁን ኢትዮጵያ ይሄንን አቅም ገንብታለች፤
👉 ባለፉት ሳምንታት በሰሜን ሸዋ እና በጎጃም ያያችሁት ዝናብ የተፈሮ ሳይሆን እኛ ያዘነብነው ነው፤
👉 በግልጽ በሚቀጥሉት ሳምንታት እናስመርቀዋልን፤ ወይንም እናስጀምረዋለን፤
👉 ኢትዮጵያ ደመናዋን ተጠቅማ ዝናብ ማዝነብ ችላለች፤
ስለህወሓት ጁንታ፣ ስለኦነግ ሸኔ እና መሰል ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የተናገሩት‼
👉 የህወሓት አመራሮችን፣ የማዕከላዊ ኮሚቴውን ሁሉ እባካችሁ ብዬ ለምኛለሁ፤ አስለምኛለሁ፤
👉  ዋና ዋና ባለሃብቶችን ታዋቂ ግለሰቦችን አሰባስቤ በሚስጥር ልኬ እባካችሁ ለምኗቸው ብዬ ሽምግልናም ልኬያለሁ፤
👉  እብሪት ከፉ ነው፤ አሁንም ያላችሁ አመራሮች ከእብሪት ልትቆጠቡ ይገባል፤
👉  በህግ ማስከበሩ ከ300 በላይ የኦነግ ሸኔ ሽፍታ አብሮ ሲዋጋ ይዘናል፤
👉  ኦነግ ሸኔ ለማንም አይበጅም፣ ለሰው ዘር አይበጅም፤ ለኢትዮጵያም ጠላት ነው፤
👉  ወለጋ ህዝብ ስቃይ ውስጥ በነበረበት አንድም ሰው አልተናገረለትም፤ ከውጭም ከውስጥም፤
👉  ኦነግ ሸኔ በሰላም ተወዳደር ሲባል እንቢ ብሎ የህውሓት ቡችላ ሆኖ ነው አርሶ አደር ገድሎ ሲፎክር የነበረው፤
👉  ወለጋ ውስጥ የሞቱት አማራ አርሶ አደሮች አማሮች አይደሉም፤ የኦሮሞ አካል ናቸው፣ እነሱን መግደል ኦሮሞን መግደል ነው፤
👉  በትግራይ ውስጥ ሰዎችን ማፈን አለ፤ ሌለው ቀርቶ እርዳታ የሚሰጡ ሰዎች ይታፈናሉ፣ ይገደላሉ፤
👉 እርዳታ እንዳይሰጡ ተደርጓል፤ በትግራይ ብዙዎች የደረሰውን በደል እያወቁም ሊክዱ ፈልጋሉ፤
👉 በአንድ ቀን በ200 ቦታዎች ላይ ነው በተጠና መልኩ በተመሳሳይ ሰአት ጁንታው ጥቃት የፈጸመው፤
👉  ኦነግ ሸኔ የኢትዮጵያ ጠላት ነው፤ ለኦሮሞ አይበጅ፤ ለአማራ አይበጅ ለማንም አይበጅም
👉  ትግራይ ውስጥ አሁን ሰው ይታፈናል፤ ርዳታ የሚሰጡ ሰዎች ሳይቀር እየታፈኑ ነው፤ ከዚህ ቀደም ካደረጉት ጥፋት በላይ አሁን የሚያደርጉት ይብሳል፤
👉  ጁንታው ያኔ 200 ቦታዎች ላይ በተመሳሳይ ሰአት አንድ ላይ ነው ጥቃት የፈጸመው፤
👉  አማራ ክልል ላይ ጥቃት የፈጸመው ይሄው ሃይል ነው፤ ዓላማውም ጎትቶ ወደ ግጭቱ ማስገባት ነው፤
👉  ኤርትራ ላይ የተኮሰው ይሄው ሃይል ነው፤ ችገሩን ቀጣናዊ ለማድረግ አስቦ ነው፤
👉  በትግራይ ከ30 ሺህ በላይ እስረኛ ተለቋል፤ መቀሌ ብቻ 10 ሺህ እስረኛ ተለቆ ዝርፊያ ፈጽሟል፤
👉  ለትግራይ ህዝብ ጦርነት ግጭት አይገባውም፤
👉  የእኛ የህግ ማስከበር ሶስት ግልጽ አላማዎች አሉት
     – በዘሩ ብቻ በማንነቱ ብቻ ለይተው መከላከያ ሰራዊትን   የጨፈጨፉትን ወንጀለኞችን ለህግ ማቅረብ ነው፤
    – ኢትዮጵያን አምነው ለ20 አመት በክልሉ የኖሩ ታግተው የተወሰዱ ከ1000 ሺህ ባለይ መኮንኖችን ማስፈታት ነው፤ መቶ በመቶ  አስፈትተናል፤ የገደሏቸውን ቀብረናል፤ የተዘረፍነውን አስመልሰናል፤
    – ይህ ክልል ወደ ምርጫ ሄዶ ራሱን እንዲያስተዳድር ነው፤ አሁን ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ በጊዜያዊ አስተዳደር ራሱን እያስተዳደረ
 ነው፤ ሊታገዝ ይገባዋል፤
👉  የተበተነው ርዝራዥ ሃይል በየቦታው እየሆነ በመከላከያ ላይ እየተኮሱ ሽንቆጣ ፈጽመዋል፤
👉  ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ማለት ነው፤ ከዚህ በኋላ ተሰብስቦ ዱቄት አይሆንም፤
👉  የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባል ሆኖ በትግራይ ክልል ወንጀል የፈጸመ ካለ በህግ ይጠየቃል፤
👉  በትግራይ ክልል ስለተፈጸመ ችግር የሚያነሱ በሰሜን ዕዝ ላይ ስለተፈጸመው ግፍ አያነሱም፤
👉  በማይካድራ ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ በኢትዮጵያ ውስጥ በየትኛውም አካባቢ አልተፈጸመም፤ ግን ተረስቷል፤
👉  ቤንሻንጉል ላይ ስላለው ጭፈጨፋ ማንም አይናገርም፤ ትኩረት ሁሉ አንድ አካባቢ የሆነው የተንሸዋረረ እይታ ስላለ ነው፤
👉  በትግራይ ከተካሄደው ኦፕሬሽን በኋላ 4.2 ሚሊዮን ህዝብ መግበናል፤
 ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን።
 
የአማራ ልዩ ሀይልን በሚመለከት የተናገሩት
👉 የህግ ማስከበር ዘመቻው ሲጀመር የአማራ ልዩ ኃይል ተደራጅቶ መሬት ለማስመለስ የገባ በማስመሰል የሚነገረው ስህተት ነው፤ ተገቢም አይደለም፤
👉 ሶሮቃና ቅራቅር ላይ ጦርነቱን የጀመረው አማራ ልዩ ኃይል አይደለም፤
👉 ልዩ ኃይሉ ባህርዳር ተቀምጦ ነው ጦርነት የተከፈተበት፤
በዚህም ምላሽ አልሰጠም፤
👉 የአማራ ልዩ ኃይል በህግ ማስከበር ዘመቻው ተጋብዞ ነው የተሳተፈው፤
👉 በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስት ስለነበርን የአማራ ልዩ ኃይል ኃላፊነት ተሰጥቶት በህግ ማስከበር ዘመቻው ተሰማርቷል፤
👉 የአማራ ልዩ ሀይል  እየሞተ ያለው ሀገር የመጠበቅ መንግስት የሰጠውን ተልእኮ እየፈፀመ ስላለ ነው፤
👉 የአማራ ልዩ ሀይልን ከፈለግን ሶማሌ ክልል  ላይ ወስደን ተልዕኮ መስጠት እንችላለን፤
👉 የአማራ ልዩ ሀይል ያጠፋው ጥፋት ካለ ታይቶ በህግ ይዳኛል፤
👉 ለጊዜው ግን ልክ ከሌላ ሀገር እንደመጣ አጥፊ ማየት ተገቢ አይደለም፤
👉 መሬትን በሚመለከት በድንበር ኮሚሽንና በፌዴሬሽን ምክር ቤት በኩል በሕግ ይፈታል
Filed in: Amharic