>
5:21 pm - Tuesday July 19, 8140

አበበ ባዩ :- የደብረ ኤልያሱ ሴኮቱሬ ጌታቸው  (አቻምየለህ ታምሩ)

አበበ ባዩ :- የደብረ ኤልያሱ ሴኮቱሬ ጌታቸው 

አቻምየለህ ታምሩ

በፎቶ   የምታዩት ግለሰብ አበበ ባዩ ይባላል። አበበ ባዩ ኢትዮ ፎረም በሚባለው የፋሽስት ወያኔ የዩቱብ ቻናል በኩል ዘግናኝ ጸረ አማራ ቅስቀሳዎችን በየቀኑ ሲያደርግ የሚውል እርመ በል ፍጥረት ነው። አበበ ይህንን ሲያደርግ የሚውለው አብዛኛው ሕዝብ አማራ በሆነበት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ደልቶት ተዘባኖ ያለ ስጋት እየኖረ ነው።
አበበ ትውልዱና እድገቱ ጎጃም ምድር ደብረ ኤልያስ ውስጥ ነው። ደብረ ኤልያስ ታላላቆቹ እነ ቀኝጌታ ዮፍታሔ ንጉሤና መላኩ በጎሰው የተወለዱበት ቦታ ነው። አገር ሲያረጅ ጃርት ያበቅላል እንዲሉ እነዚያን የብዕርና የጸረ ፋሽስት ጣሊያን አርበኞች ያፈራው ደብረ ኤልያስ ዛሬ ላይ አበበ ባዩ የሚባልን በአማራ ሕዝብ ላይ የፋሽስት ወያኔን ዘግናኝ ጸረ አማራ ቅስቀሳ ሲያቀርብ የሚውል እርመ በል የሆነ ጃርት አብቅሏል።
አበበ ባዩ በአማራ ሕዝብ ላይ ያላካሄደው የፍጅት ቅሰቀሳ የለም። በትግራይ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ያካሄደ፣ የትግራይን መሬት መርሮ የያዘ ተስፋፊ፣ ከሻዕብያ ጋር በማበር ትግራይን ያጠፋ፣ ትግራይን በመክበብ በርሀብ እንዲያልቅ ያደረገ፣ የትግራይ ሕዝብ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ያለውን አስተዋጽኦ ለመፋቅ አስቦ የሚሰራ፣ ወዘተ የሚሉት የፈጠራ ውንጀላዎች አበበ ባዩ በየቀኑ በአማራ ሕዝብ ላይ በኢትዮ ፎረም በኩል ሲያሰራጫቸው ከሚውላቸው የጽልመት ቅስቀሳዎች መካከል ዋናዋናዎቹ ናቸው።
ባጭሩ አበበ ባዩ በአሁኑ ጊዜ ኢትዮ ፎረም በተባለው የፋሽስት ወያኔ ቻናል ውስጥ ተቀጥሮ የሚሰራ ደብረ ኤልያስ ውስጥ የተወለደ የትግሬ ብሔርተኛ ነው። ኢትዮ ፎረም በአበበ ባዩ በኩል በአማራ ሕዝብ ላይ የሚያሰራጨው የጅምላ ጭፍጨፋ ቅስቀሳ የሩዋንዳን የዘር ፍጀት አነሣስቶ ያስፈጸመውን Radio Télévision Libre des Milles Collines (RTLM) ያስንቃል። አበበ ኢትዮጵያንና የአማራን ሕዝብ በመጥላት ጣሊያናዊውን ፋሽስት ግራዚያኒን የሚያስንቀው የአገር በቀሉ ጥቁር ግራዚያኒ የመለስ ዜናዊ አምላኪ ነው።
ፋሽስት ወያኔ በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ማካሄድን ፖለቲካው ያደረገ የጽልመትና ደም አፍሳሽ ድርጅት ነው። በሰሜኑ ያገራችን ክፍል ፋሽስት ወያኔ እያካሄደ ያለው ፍጅት፣ ውድመትና የዘር ማጥፋት ለማስቆም ሕዝባችን ፊትለፊት ሲዋደቅ አበበ ባዩ ግን አዲስ አበባ ተቀምጦ የፋሽስት ወያኔ አፈ ቄሳር በመሆን አማራን ከኋላው እየወጋ ያለ ስጋት ይኖራል።
ለመስማት እንኳ በሚሰቀጥጥ አኳኋን በአማራ ሕዝብ ላይ የፋሽስት ወያኔን የፍጅት ቅስቀሳ ሲያካሂድ የሚውለው አበበ ባዩ  እንደ መንፈስ አባቱ ሴኮቱሬ ጌታቸው ከፋሽስት ወያኔ ጋር ወደ ደደቢት ወርዶ ጸረ አማራ ቅስቀሳውን ያካሂድ እንጂ አዲስ አበባ ተቀምጦ በየሰዓቱ ዘግናኝ ጸራ አማራ ቅስቀሳ እንዲያካሂድ ሊፈቀድለት አይገባም።
በአማራ ላይ የእልቂት ዘመቻ እያካሄደ ነፍሱን ለፋሽስት ወያኔ ሽጦ በሚከፈለው የደም ገንዘብ ኑሮውን የሚገፋው አበበ ባዩ በየቀኑ በሚያሰራጨው ጸረ አማራ ቅስቀሳ፤ አማራውን ለብዙ ሺህ ዓመታት ይኖርበት ከነበረው ከአጽመ ርስቱ ሲያፈናቅል ለኖረው፣ ሲገድል እና ሲያስገድል ለነበረውና አሁንም ለሚያስገድለውና ለሚያፈናቅለው ፋሽስት ወያኔ ለማገልገል ስለመረጠ በሚያሰራጨው ጸረ አማራ ቅስቀሳ ሁሉ ኃላፊነት አለበት። አበበን  አማራም ኾነ ጸረ አማራ የሚያደርገው ተግባሩ ነው። አማራን በሚመለከት በተግባር በአበበ ባዩ እና በግራዚያኒ መካከል ከቆዳ ቀለም በቀር ምንም ልዩነት የለም።
በመሆኑም አበበ ባዩ የፋሽስት ወያኔ አፈ ቄሳር ሆኖ ፋሽስት ወያኔ በአማራ ሕዝብ ላይ እያካሄደ ያለውን የጅምላ ፍጅትና የዘር ማጥፋት አጠናክሮ እንዲቀጥል እያደረገ ባለው ጸረ አማራ የጥላቻ ቅስቀሳ፣ ፋሽስት ወያኔ እያካሄደ ላለው የአማራ የጅምላ ፍጅት፣ ውድመትና የዘር ማጥፋት እየሰጠ ባለው ከፍተኛ የፕሮፓጋንዳ ድጋፍና ለአለማቀፍ ወንጀለኛውንና አሸባሪውን ፋሽስት ወያኔን በመርዳት እያደረሰ ላለው የሕይዎት መጥፋትና የንብረት ውድመት የአማራ ሕዝብ ሊፋረደው ይገባል።
ቤተሰቦቹና ጓደኞቹም ነፍሱን ለፋሽስት ወያኔ ሽጦ በአማራ ሕዝብ ላይ ከመጠን ያለፈ የጥላቻ ቅስቀሳ ማካሄደን የሕይዎት ጥሪው ያደረገውን አበበ ባዩን አውግዘው ከሱ መራቅና ፍርዱን እንዲያገኝ ማድረግ አለባቸው። በአማራ ሕዝብ ላይ ከመጠን ያለፈ የጥላቻና የጅምላ ፍጅት ቅስቀሳ አካሂዶ ፋሽስት ወያኔ በከፈለው የደም ገንዘብ ያፈራው የወንጀል ሀብትና ንብረትም ተወርሶ የፋሽስት ወያኔ የሽብርና የጅምላ ጥቃት ሰለባዎች ለሆኑት ግፉዓን መሰጠት አለበት።
Filed in: Amharic