>

ማነው ይሄ ፍፁም በግ ፍፁም ተኩላ? (ሊዲያ ዘ ጊዮን)

አብይ አህመድ የዘር ሀረጋቸው ከአማራ እናት እና ከኦሮሞ አባት ይመዘዛል:: የሀይማኖታዊ ተዋቅሮዋቸው ደግሞ ቦራክ ኦባማዊ ነው! በስማቸው ያነገቡት የሞስሊም ሀይማኖት ስም ሲሆን በእናታቸው ደግሞ ኦርቶዶክሳዊውን እምነት በውርስ ሲያገኙ እሳቸው እራሳቸው ግን በግል ጉዞዋቸው ወደ ፕሮቴስታን አስተምሮ ፊታቸውን ያዞሩ በናንተ በብዙሀን አባባል “ጼንጤ” ናቸው ማለት ነው::

አብይ መሀመድ ዊኪፒዲያ የግል ፕሮፋይላቸው ለማወፈር ይመስላል ያልታጨቀ ጉዳይ የለም በትንታኔ ቀጫጭነቱ እንዳለ ሆኖ መነፋፋቱን ግን እውነታነቱን አጠያያቂ ያደርገዋል!

እኝሁ ሰው አንዳንድ ባገኙኃቸው መረጃዎች እንደሚያሳዩት በውጭው ሀይል ታጭተው በምእራባዊያን globalist አጅንዳ የተጠመቁ መሆናቸውን ያጋልጣል! በዚሁ ጥምቀትም ሞስሊምም ኦርቶዶክስነትንም ፕሮቴስታንትነትንም ኦሮሞ አማራነትንም ክደው እንደሆን ልብ ይባል!

እናም ዱካ በዱካ ብዙ ማበጠር ሳያስፈልገኝ ብዙ አወዛጋቢ ነገሮችን ለማግኘት ችያለው! የሚያራምደውን አጀንዳም ስፈትሽ መረጃው እውነትነት እንድቀበል አስገድዶኛል::

ለማ መገርሳ በአለም አቀፋዊ መድረክ ላይ ቀርቶ በኢትዮጵያ ላይ በፖለቲካው ምህዳር ላይ እንዲገዝፍ ያደረገው ያማራው ከሚናው ውጭ መደረግና ብሎም የሚዲያ ሽፋን በሰፊው በመስጠት ትልቅ ሚናን እንደ ተጫወተ ማስመስውል ተችሏል:: እንጂማ ንግግሮቹ እንኳን በሀገር ደረጃ በጥሩ በገባቸው ልጆች የጫት መደብ ላይ እንኳ የሚወራ አይደለም! እና ለማን ወደፊት አምጥቶ በመለስ ጫማ አስጫምቶ ለማስኬድ ትንሽ ይከብዳል! የመለስ ጫማ ያን ያህል ትልቅ ሆኖ ሳይሆን የለማ እግር ቀጫጫነት ለዛች ድንክ ጫማ እንኳ አትበቃምና ነው:: መለስ ጥሩ ሎሌ በደንብ በምእራቡ አለም አጀንዳ የተቃኘ እና ትእዛዝን ሳያዛንፍ የሚያስፈፅም ፍፁም ተኩካ ፍፁም በግ ሆኖ መታየት የቻለ ተንከሲስ ነበር!

ወደ አብይ ስንመለስ ይሄ ሰው ቦራክ ኦባማዊ ማንነት ተገንብቶለት የምእራቡ አለም ግሎባሊስቶች አስተካክለው ያቆሙት ሰው ለመሆኑ ብዙ ሳትዳክሩ የሚኮርጃቸውና የሚያጠናጥንባቸውን ጉዳዩች ከዚህ ከቋጠርኳቸው ማስረጃ የምስል ቅንብሮች በመጨቆን በደንብ ግንዛቤ ማግኘት ይቻላል!

በእርግጥ ኢትዮጵያን በማፍረስ እቅድ ተግባር ላይ ይህንን ሰው ከመለስ በሚስተካከል መልክ ለመቅረፃቸው ምንም ጥርጥር የለኝም!

እንግዲህ ቦራክ ኦባማን ስንወስድ ሞስሊም ማህበረሰቡ ሞስሊም በመሆናቸው በሁሴን ስማቸው ጨርቁን እንደ ጣለላቸውና የመጀመሪያም ሞስሊም ስም ይዞ በአሜሪካን ላይ በመግስት ወንበር የተቀመጠ ተብሎ ብዙ ተጨፈረላቸው! ጥቁሩም የመጀመሪያ ጥቁር ሰው አገኘን ብሎ ጨርቁን ጣለ! ያለ የሌለውን ድምፅ በነቂስ ወጥቶ ሰጣቸው ለንግስናቸው ግብር ሲከፍል! ከዛም ፕሮቴስታንቱ ያዙኝ ልቀቁኝ አለ ጥቁር የሆነ ከሞስሊምነት ወደ ፕሮቴስታንትነት በድል የመጣ የኛ መሲህ ኡኡ አለ በላያቸውም ወስዶ ከባድ አንገታቸው ሊሸከመው የማይችልን ዘውድ ደፋባቸው! እርሳቸው ግን ጥቁርም ነጭም ክርቲያንም ሞስሊምም አልነበሩም!

በቀዳሚነት ከሊቢያ በጀመረ ጠንካራ የሞስሊም መሪዎችን ማዳከሙን ስራ ቤንዚኑን ገፋ ሞቅ በማድረግ ፍጥነቱን ጨመር አድርገው አራምደው ለጋዳፊ መንግስት መንኮታኮት በትልቁ አዋጡ! ትልቅ ግንድ በጥሰው ጣሉበት ሞስሊሙ አይኑ እያየ! ሲለጥቅም ሲሪያን ካልወጋሁ አሉ ህዝብ እንዴት ተብሎ ብሎ መሄዱን ፍቃድ ቢንፍጋቸው በጀመሩት መንገድ በሜርሲነሪዎቻቸው ሲሪያ እያየን እንደ ጉም ተነነች ያች የታሪክ አምባ የኛን ሁሉ ታሪክ የያዘች ምድር! በዚህችው አገር በዋናነት የተጨፈጨፉ ክርስቲያን ኦርቶዶክሶች ናቸው! እነሱን ካስጨረሱ ኃላ ሞስሊሙን ቀሉት ስደተኛ አደረጉት ባይተዋርነትን አሸከሙት!

ሲለጥቅ ደግሞ የጥቁሩን ማህበረሰብ ከትምህርት ቤቶቹን ከመዝጋት ያነሳ በአደባባይ እንደ በሬ በፖሊሶች መጎተት መገደል በሳቸው ግዜ ይበልጡን ለየለት! የህክምና ወዘተ ዘርፎች ላይ በተሀድሶ ስም ደሀውን ጥቁር ሌላ ባርነት ጣሉበት! አዳኝ አገኘው ያለው ጥቁር ማህበረሰብ ግራ ተጋባ ብሎም ሌላ የስነልቦና ቀውስ ተከናነበ! ፕሮቴስታንቱንም መሲህህን ወዲያፈልግ ሲሉ የግብረ ሰዶማዊያንን ጋብቻ ፈቀዱለት! እግዜር ህግ ባህል አትበልብኝ እናንተ judgmental እያሉ የእግዚያብሄርን ቃል እና ትዛዝ በፍርደ ገምድል ፈራጅነት ኮንነው እሳቸው መሲህነታቸውን በአንድ ፆታ ያሉ ሰዎችን የጋብቻ መብት መጠበቅ መሲህነታቸው ለጨለማው አለም መሆኑን አስመሰከሩ! እርፍ!

እናም ዛሬ ፍፁም በግ ፍፁም ተኩላ ሆኖ የብርሀን መላእክ እስኪመስል ሊያስት የመጣው የኛ ቦራክ ኦባማ ደግሞ እወክለዋለሁ የሚለውን ጥርቅምቅም ማንነት በተሸራረፈ በእምነትም ይሁን በዘር ያገኘውን ማንነትን ተገን አድርጎ የግሎባሊስቶችን አጀንዳ ሊያስፈፅም እወክለዋለሁ በሚለው በዛው ዘርፈ ብዙ ዘርና ሀይማኖት ላይ በዚሁ ሰው እንዲወጋ ይሆናል ማለት ነው!

በነኝህ ሊንኮች ላይ የኝህን ሰው አርቲፊሻል ማንነት ቀረፃን መመልከት ይበጃል! በቴሌ ፕሮፕተር ልክ ተደግፈው ቃልን ከነ ሄንሪ ኪሲንጀር ቃል በቃል ሲሰርቅና አዋቂ ሊባል ሲዳዳው እዩልኝ!

https://en.wikipedia.org/wiki/Abiy_Ahmed_Ali

https://t.co/VDlJg4mBQj

Full version https://t.co/VDlJg4mBQj

ከዚህ በታች ያለውን የሄንሪ ኪሲንጀር ቃል አፍ በአፍ ቃል በቃል በቴሌ ፕሮፕተር ተደግፎ እያወራ ካሜራ ያዡም እሱን እየለየ እንዲቀርፅ ተደርጎ የሚያጭበረብርበትን ይህንን ቪዲዮ ለግንዛቤ ተመልከቱ! አክሰንቱ ላይ የሚሰራው ሌላ ድራማ ምን ያህል mediocrity የተጠናወተው ፍፁም በግ ፍፁም ተኩላ መሆኑን ያስገነዝባል!

“The world is in chaos. Fundamental upheavals are occurring in many parts of the world simultaneously, most of which are governed by disparate principles.”

That’s what Henry Kissinger said in this interview http://jworldtimes.com/…/in…/the-lessons-of-henry-kissinger/

“My instinct is—and I hope I am right—that an American president who presents a framework combining fortitude and purpose will be supported ”

That’s what kissinger said again
https://www.theatlantic.com//kissinger-order-and-c…/506876/

” I am, but I believe in evolutionary stability. I do not believe you can ever maintain the status quo in perpetuity. The challenge, then, is to devise a system in which change can be accommodated without producing chaos ”

https://www.theatlantic.com/…/kissinger-order-and-c…/506876/

“fear and desire are the twin engines of human survival but with most of our basic needs met these instincts are being engaged to imprison us…..” Russel Brand
https://www.newstatesman.com//…/russell-brand-on-revolution

“Every society that has ever existed in human history has at some point declined. You can be arrogant enough to believe that it cannot happen to you, but you need the humility to recognize the limitations of human foresight. That said, you must have some faith in yourself. Lack of faith in a society is an early symptom of decline.”

https://www.theatlantic.com/…/kissinger-order-and-c…/506876/

https://ethiobook.net/ማነው-ይሄ-ፍፁም-በግ-ፍፁም-ተኩላ-ሊዲያ-ዘ-ጊዮን

Filed in: Amharic