ዛሬ ሰኔ 9 ቀን 2010 ዓ.ም በቡኖ በደሌ ዞን ደዴሳ ወረዳ የአማራ አርሶ አደር ከብቶች በስለት መወጋታቸውንና ውጡ መባላቸውን ገልፀውልኛል። በትናንትናው ዕለት በተደራጁ ወጣቶች ዛቻና ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው እንደሆነና ሰብላቸውን መሰብሰብ እንዳልቻለሁ ለወረዳ አስተዳዳሪው አቶ በድሩ ሙዘይን በቃል አቤቱታ ቢያቀርቡም “እና እናንተ መሬቱን ለምን አትለቁም ” የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ነግረውኛል። በክረምት ሜዳ ላይ የሚወድቁ የአማራ ገበሬዎች ከፕሮፓጋንዳ ያለፈ የተግባር ምላሽ ያስፈልጋቸዋል።
የፕሬዚዳንቱ መመሪያ "እንዳያማህ ጥራው እንዳይበላ ግፋው" እየሆነ ይመስላል!!! (ኢ/ር ይልቃል ጌትነት)
Filed in: Amharic