ሳሙኤል ገዛህኝ በላቸው
ይህ የተንዛዛ እና የተግተለተለ ሀረግ ህወሃት ህዝብን ለማታለያ እና ለክህደት ዓላማው መጠቀሚያ እንዲሆን ያጨቀው ነው:: (ኦነግም ተባባሪ ነበር)
የህገ-መንግስቱ መግቢያ (preamble) የሚጀምረው በነዚህ በተምታቱና በተጭበረበሩ ሀረጎች ነው እኛ በማለት:: እነዚህ ህወሓት ሰራሽ የተግተለተሉ ሀረጎች የህገ-መንግስቱ (የቃልኪዳን ሰነድ) ባለቤት ናቸው ይለናል::
እነማን ብሄር እነማን ብሄረሰብ እነማን ህዝቦች እንደተባሉ አይታወቅም:: አሁን ህወሓትም የሚያውቀው አይመስለኝም::
በህገ-መንግስቱ የተገለፀና የአንቀፅ 39 አጃቢ ተደርጎ ጎጠኞች ደጋግመው የሚጠቅሱት: አንድ ሌላ ተቀፅላ አለ ‘በህዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሰረተች አገር’ የምትል ሀረግ::
በእርግጥ እነዚህ የተፈቃቀዱትና ፈቃዳቸውን የሰጡት እነማን ናቸው? የነማን ፈቃድ ነው ኢትዮጵያን ትሁን ትኑር ብሎ ያቆማት ? ብለን እንጠይቅ::
እንደ ክህደቱ: አንዳንድ ህዝብ እና ብሄር ተብለው የተጠቀሱት አስቀድመው ራሳቸውን የቻሉ: በራሳቸው የቆሙ: እንደ ሀገር መሪ ስርአት እና ግዛት የነበራቸው ናቸው ይሉናል:: እነዚህ ህዝብና ብሄር ደረጃ ደርሰዋል ተብለው የተሰየሙት አሁን የክልልነት መብት እና ቁመና የተሰጣቸው ናቸው:: በኃላ ላይ የተደፈጠጡትን ወደ 8እና 9 ግድም በደቡብ የነበሩ ክልሎችንም አስቧቸው::
ኢትዮጵያን እና ህገ-መንግስቱን ፈቅደው የመሰረቱት እነዚህ ክልሎች ሉዓላዊ አገራት ነበሩም ይሉናል:: በዚህም መሰረት ኦሮሚያ የሚባል: ከጭንሀክሰን እስከ ደምቢዶሎ: ከሞያሌ እስከ ጎሀ ፅዮን የተዘረጋ አገር: አማራ የሚባል: ከደባርቅ እስከ ደጀን: ከባህርዳር እስከ ወልድያ የተዘረጋ አገር: ትግራይ የሚባል: ከዛላምበሳ እስከ አላማጣ: ከሁመራ እስከ እስከ መቀሌ የተዘረጋ አገር: ሶማሌ የሚባል: አፋር የሚባል: ቤንሻንጉል የሚባል: ጋምቤላ የሚባል: ሀረሪ የሚባል እንዲሁም በኃላ የተጨፈለቁት በደቡብ ያሉ 9 ሉዓላዊ አገራት ነበሩ ይሉናል:: እነዚህ ሉዓላዊ ሀገራት ፍቃደኛ ሆነው ኢትዮጵያን መሰረቱ ነው የተረቱ ማጠንጠኛ::
ኢትዮጵያዊ ዜግነት ብቻውን አይቆምም: ኢትዮጵያዊ ማንነትም የለም የሚለው ክህደታቸው መሰረት የሚያደርገው ይሄን ‘የብሄር በሄረሰቦችና ህዝቦች’ ተረት ነው:: ከኢትዮጵያዊ ዜግነት ይልቅ የአማራ አገር ዜጋ: የኦሮሞ አገር ዜጋ…ወዘተ ናቸው ያሉት ይሉናል::
ግን ይህ ሁሉ ክህደት አላማው ምንድነው? ለምን አስፈለገ ? በቀጥይ እናየዋለን::
ኢ ት ዮ ጵ ያ እ ና ኢ ት ዮ ጵ ያ ዊ ነ ት
ለ ዘ ላ ለ ም ይ ኑ ር !!