ስልጣን ጥመኞቹ ያልተቀደሰ ጋብቻና ሙሾ አውራጅ ሚድያዎች !!!
ካሳሁን ለማ
ይህንን አስተያየት ስፅፍ በዓለም ኡቀፍ ደረጃ አንድ ሚሊየን   አንድ መቶ  ሃምሳ አራት ሺ ስዎች ከቫይረሱ እገግመዋል ወይም ድነዋል::
መገናኛ ብዙኃን በቫይረሱ የተያዙቱንና የሞቱቱን ብቻ አጉልቶ በመዘገባቸው ለማሕበራዊ ቀውስ መፈጠር ምክንያት ሊሆን እንደሚችል በSociety ጉዳይ ላይ ጥናት ያደረጉ የመስኩ ባለሞያዎች አየሰጉ ይገኛሉ::
ሁልጊዜ  አሉታዊዉን አጉልቶ  በማሳየት ሚዲያዎች መሥራታቸው ከሚገኘው ጥቅም ይልቅ  ውሎ አድሮ የሚያስከትለው  ጥፋት ሊኖር ግድ ነው::በኢትዮዽያ  ፖለቲካ ውስጥ እየታየ ያለ እውነታ  ይኸው ነው !
ጃዋርና ልደቱ ታሪካዊ ፖለቲካዊ ጋብቻቸውን OMN በሚባለው የዘር ጥላቻ  አመንዣጊ ሚዲያ መስኮት ላይ መታየታቸው ማሕበራዊ ሚዲያው እየተንጫጫባቸው መሆኑ ተሰምቷል::
በዚህ ያልተቀደሰ ጋብቻ  ባለድሎቹ ወይም ተጠቃሚዎች  በኪሳራ ወድቀው ለማንሰራራት  ቆስለው ደፋ ቀና ሲል ለነበረው Jዋርና OMN ነው::ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው ከ97 ምርጫ በኃላ በደረሰበት የፖለቲካ ክስረት አፈር ልሶ ወደ ሕዝብ ጉያ በመመለስ ነጥብ አስቆጥሮ  ወደ ቀደመ ቦታው እየተመለሰ ቢሆንም;በዚህ ወሳኝ  ወቅት በሕዝብ በተተፋው ጅዋር ና  የርስበርስ ጦርነት ናፋቂው OMN ስክሪን ላይ በመታየቱ የእስከዛሬ  ጥረቱ በሰከንዶች ነጋቲቭ ዜሮ ላይ ወርዷል:: እንደሚታወቀው ጃዋር  ለ86 ነብስ  መጥፋት ; ልደቱ ደግሞ በ1997 ምርጫ ጋር በተያያዘ ከመቶዎች በላይ ንፁኃን ነብስ እጁ በአሉታዊ ሚናው ሲጠቀስ ቆይቷል::
የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ ለመዘወር የሚነሱትና የሚወድቁት በአካልም የምናቃቸው በጣም ጥቂቶች ናቸው::እነዚህ ሊህቃን በዘርና ሥልጣን ሥር የሌለው ምሶሶ ላይ የተንጠለጠሉ ናቸው::ሁለት ጣት የምትሆን ሚዲያ አላቸው::እንዲሁም ቁጥሩ ያልተገደበ የሶሻል ሚዲያ አካውንትና በፈለጉት ጊዜ የዘረፉትን ብር እየከፈሉ ዱላ ይዞ የሚወጣ ከተጨባጩ የኢትዮጵያና የአለም ሁኔታ  የራቀ የፈረደበት ቄሮ አላቸው::ከዚህም በመለጠቅ በLike Shareና Subscribe በቁጥር  ከሌላው ለመብለጥ የተሰለፋ Youtubers ጨምሮ ሌሎች Social mediaዎች ጩኸቱን በማጎን እያወቁ ተጠቃሽ አጨቃጫቂ  ፖለቲከኞችን ድምፅ ያለቦታው ያስጮኃሉ ::ያኔ አገሪቱ ፖለቲከኛ እንደሌላት ተደርጎ  በጥቂቶች ሶሻሉም መደበኛውም ይሰለባል::
በመግቢያዬ እንደገለፅኩት አሉታዊዉን በማግዘፍ  ዓለም በኮረና ቫይረስ  ምክንያት እንዳለቀላት ተደርጎ የተዘገበው  ኢ-ፍትሃዊ የሚዲያ አቀራረብ አንድምታው በሌላ ፖለቲካዊ ጨዋታ በቁጥር  እንኳን አስራአምስት የማይሞሉ ዘረኛና  ሥልጣን ወዳድ አጭበርባሪዎች  ባፉለጋቸው መንገድ እንዲፈነጩ ረድቷቸዋል::እነዚህ አስራ … ምናምን ሰዎች ከትግራይ ;ከኦሮምያና አዲስ አበባ መሆናቸው ልብ በሉልኝ::
ልደቱ በአንዴ OMN መስኮት የመጨረሻውን ማስተዛዘኛ  ለመቁረጥ የተዘጋጀ ያህል ነው – ቃለ ምልልስ ሲጠቃለል የሚንግረን::እንደ ልደቱ ከመስከረም 30 በኃላ በኢትዮጵያ መንግስት የለም::አነጋገሩ  ጃWarንና ፅንፈኞችን ለመቀላቀሉ የፊርማ ሰነድ ይመስላል::በርግጥም ነው !
ኢትዮጵያ የፖለቲከኛ ደሃ እይደለችም::የኢትዮዽያን ተጨባጭ ሁኔታ ተንተርሰው አፊሪካና ዓለምን ተንትነው በዝርዝር  የሚያስቀምጡ  አዕላፍ ፖለቲከኞች  ከዳር እስከ ጥግ አላት::ጥቂት ባለ ጊዜ ብሔርተኞችና የአቋራጭ ሥልጣን ናፋቂዎች ሚዲያን ተሸሽግው ሊደፍሯት ሞከሩ እንጂ !
ልደቱ አያሌው ስለ ጃዋር “ፖለቲካዊ ተጠያቁይዊነት” የተንገረውን መጥቀሱ ጊዜ መፍጀት ነው;;ጃዋርም በአሽሙር የተናገረውንም ማቅረብ ይቻላል::በእነዚህ ሽምጥ ጋላቢዎች ላይ ብዙ መናገር ይቻላል::የመልዕክቴ ነጥብ ግን ያ ! አይደለም::
ፖለቲከኞች ስግብግቦችና ራስ ወዳዶች ናቸው::በተለይ ሚዲያ ካገኙ  የሚናገሩትን አያውቁም::ልደቱ አያሌው  ፖለቲከኛ መሆን ከጀመረበት አንስቶ እስከ OMN ያለውን ቃለ መጠይቅ Perspective ፈፅሞ ረስቶታል ወይም ሥልጣን ከመመኘት ራዕዩ አኳያ ሲታይ “ደንዝዟል” ብል ትክክልኛ አቀራረብ ነው ::
ችግሩ የኢትዮዽያ ሚዲያ ዜና ወይም ታሪክ እመራረጥ ነው;;ባጭሩ ሚዲያዎች  ለአገር; ለሕዝብና  ለመጪው ትውልድ ከመጨነቅ ይልቅ  ለዕለቱ ላይክ;ሼርና ሰብስክራቭ ሲጨናነቁ ተስተውሏል::
በጣም  ጥቂቶችን ከፍ አናድርጋቸው::ባለ ራዕዮችን ከፍ እናድርጋቸው::Jዋርና ልደቱ  እንደ ኮረና ተጠቂዎቾና ሟቾች  ለማገንን የምትሞክሩትን ያህል ;
ኢትዮዽያ በማንኛውም ቅፅበት ተሯርጠው ከተጠቃሽ አንድ ፍሬ ጥሬዎች የበለጡ ፈጥኖ ደራሾች አሏት!
… ይሁንና አሁን ደግሞ የጃዋር ሲገርመን የልደቱ አዲስ ትርክት የኢትዮዽያ መፃኢ በማጨለም ተጀምሯል::በፖለቲካው አቋም ረገድ ጃዋርና ልደቱ ማዶ ለማዶ ናቸው::ስልጣንን በአቋራጭ ለመያዝና ሕዝብን ለማንሳሳት በዕኩይ የሴራ ፖለቲካ በአንድ ላይ መሰለፍ አማራጭ የሌለው ጋብቻ እንደሆነ አምነውበት ወደ አደባባይ ዉጥተዋል::እዚህ ላይ ችግሩ ሚዲያዎች ሁኔታውን ( በተለይ ዩ ቲዩብ ) በማራገብ ሁለት ፍሬ የማይሞሉ እፍኝቶችን  በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ  ወሳኝ እንደሆኑ በማስመሰል ሁኔታውን ማጮሁ ተገቢ አልነበረም:መልካምና ለአገር ግንባታ ጠቃሚ  የሆኑ ታዋቂ ፖለቲከኞች ; አክቲቪስቶችና የማሕበራዊ ሚዲያ  አቀንቃኞችን ድምፅ ማጉላት ለሁለንተናዊ  ዕድጉትና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት  አስተዋፅኦቸው በአረንጏዴ ቀለም መሠመር አለበት::
እንደኔ የኮረና ቫይረስ አዲስ ተጠቂና ሟች እየተለየ የሚጮህለትን ያህል ከህመሙ የተፈወሱና ቫይረሱን ለማጥፋት ፊት ለፊት የገጠሙ የህክምና ሳይንቲስቶች;ዶክተሮችና ነርሶች ገድል እምብዛምብ አይፃፍም ወይም አይወሳም::በኢትዮዽያ ሚዲያዎች የሚስተዋለው ነጭ ሃቅ ይኸው ነው ::
ኢትዮዽያ በአሁኑ ሰዓት አሁን ያለውን የአገራቱን ፖለቲካና ህገ መንግስት የሚተነትኑ  በርካታ  ፖለቲከኞችና ተንታኞች አሏት::ዕድሉ ሊሰጣቸው ይገባል!
ለሁለት ፍሬ ሥልጣን ናፋቂዎች ያን ያህል መንጫጫት ተገቢነቱ አይታየኝም::ኢትዮዽያ ትልቅ አገር ናት::
የኢትዮዽያ ሕዝብ ያለ;የሚኖርና የሚቀጥል ታሪክ ያለው ሕዝብ ነው::ከመስከረም ሰላሳ በኃላም ጥቅምት አንድ ነው::
ለሀገር በጎ ራዕይ ያላቸው ድምፃቸው ይሰማ !
