>

ስልጣን ጥመኞቹ  ያልተቀደሰ ጋብቻና ሙሾ አውራጅ ሚድያዎች !!! (ካሳሁን ለማ)

ስልጣን ጥመኞቹ  ያልተቀደሰ ጋብቻና ሙሾ አውራጅ ሚድያዎች !!!

ካሳሁን ለማ
ይህንን አስተያየት ስፅፍ በዓለም ኡቀፍ ደረጃ አንድ ሚሊየን   አንድ መቶ  ሃምሳ አራት ሺ ስዎች ከቫይረሱ እገግመዋል ወይም ድነዋል::
መገናኛ ብዙኃን በቫይረሱ የተያዙቱንና የሞቱቱን ብቻ አጉልቶ በመዘገባቸው ለማሕበራዊ ቀውስ መፈጠር ምክንያት ሊሆን እንደሚችል በSociety ጉዳይ ላይ ጥናት ያደረጉ የመስኩ ባለሞያዎች አየሰጉ ይገኛሉ::
ሁልጊዜ  አሉታዊዉን አጉልቶ  በማሳየት ሚዲያዎች መሥራታቸው ከሚገኘው ጥቅም ይልቅ  ውሎ አድሮ የሚያስከትለው  ጥፋት ሊኖር ግድ ነው::በኢትዮዽያ  ፖለቲካ ውስጥ እየታየ ያለ እውነታ  ይኸው ነው !
ጃዋርና ልደቱ ታሪካዊ ፖለቲካዊ ጋብቻቸውን OMN በሚባለው የዘር ጥላቻ  አመንዣጊ ሚዲያ መስኮት ላይ መታየታቸው ማሕበራዊ ሚዲያው እየተንጫጫባቸው መሆኑ ተሰምቷል::
በዚህ ያልተቀደሰ ጋብቻ  ባለድሎቹ ወይም ተጠቃሚዎች  በኪሳራ ወድቀው ለማንሰራራት  ቆስለው ደፋ ቀና ሲል ለነበረው Jዋርና OMN ነው::ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው ከ97 ምርጫ በኃላ በደረሰበት የፖለቲካ ክስረት አፈር ልሶ ወደ ሕዝብ ጉያ በመመለስ ነጥብ አስቆጥሮ  ወደ ቀደመ ቦታው እየተመለሰ ቢሆንም;በዚህ ወሳኝ  ወቅት በሕዝብ በተተፋው ጅዋር ና  የርስበርስ ጦርነት ናፋቂው OMN ስክሪን ላይ በመታየቱ የእስከዛሬ  ጥረቱ በሰከንዶች ነጋቲቭ ዜሮ ላይ ወርዷል:: እንደሚታወቀው ጃዋር  ለ86 ነብስ  መጥፋት ; ልደቱ ደግሞ በ1997 ምርጫ ጋር በተያያዘ ከመቶዎች በላይ ንፁኃን ነብስ እጁ በአሉታዊ ሚናው ሲጠቀስ ቆይቷል::
የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ ለመዘወር የሚነሱትና የሚወድቁት በአካልም የምናቃቸው በጣም ጥቂቶች ናቸው::እነዚህ ሊህቃን በዘርና ሥልጣን ሥር የሌለው ምሶሶ ላይ የተንጠለጠሉ ናቸው::ሁለት ጣት የምትሆን ሚዲያ አላቸው::እንዲሁም ቁጥሩ ያልተገደበ የሶሻል ሚዲያ አካውንትና በፈለጉት ጊዜ የዘረፉትን ብር እየከፈሉ ዱላ ይዞ የሚወጣ ከተጨባጩ የኢትዮጵያና የአለም ሁኔታ  የራቀ የፈረደበት ቄሮ አላቸው::ከዚህም በመለጠቅ በLike Shareና Subscribe በቁጥር  ከሌላው ለመብለጥ የተሰለፋ Youtubers ጨምሮ ሌሎች Social mediaዎች ጩኸቱን በማጎን እያወቁ ተጠቃሽ አጨቃጫቂ  ፖለቲከኞችን ድምፅ ያለቦታው ያስጮኃሉ ::ያኔ አገሪቱ ፖለቲከኛ እንደሌላት ተደርጎ  በጥቂቶች ሶሻሉም መደበኛውም ይሰለባል::
በመግቢያዬ እንደገለፅኩት አሉታዊዉን በማግዘፍ  ዓለም በኮረና ቫይረስ  ምክንያት እንዳለቀላት ተደርጎ የተዘገበው  ኢ-ፍትሃዊ የሚዲያ አቀራረብ አንድምታው በሌላ ፖለቲካዊ ጨዋታ በቁጥር  እንኳን አስራአምስት የማይሞሉ ዘረኛና  ሥልጣን ወዳድ አጭበርባሪዎች  ባፉለጋቸው መንገድ እንዲፈነጩ ረድቷቸዋል::እነዚህ አስራ … ምናምን ሰዎች ከትግራይ ;ከኦሮምያና አዲስ አበባ መሆናቸው ልብ በሉልኝ::
ልደቱ በአንዴ OMN መስኮት የመጨረሻውን ማስተዛዘኛ  ለመቁረጥ የተዘጋጀ ያህል ነው – ቃለ ምልልስ ሲጠቃለል የሚንግረን::እንደ ልደቱ ከመስከረም 30 በኃላ በኢትዮጵያ መንግስት የለም::አነጋገሩ  ጃWarንና ፅንፈኞችን ለመቀላቀሉ የፊርማ ሰነድ ይመስላል::በርግጥም ነው !
ኢትዮጵያ የፖለቲከኛ ደሃ እይደለችም::የኢትዮዽያን ተጨባጭ ሁኔታ ተንተርሰው አፊሪካና ዓለምን ተንትነው በዝርዝር  የሚያስቀምጡ  አዕላፍ ፖለቲከኞች  ከዳር እስከ ጥግ አላት::ጥቂት ባለ ጊዜ ብሔርተኞችና የአቋራጭ ሥልጣን ናፋቂዎች ሚዲያን ተሸሽግው ሊደፍሯት ሞከሩ እንጂ !
ልደቱ አያሌው ስለ ጃዋር “ፖለቲካዊ ተጠያቁይዊነት” የተንገረውን መጥቀሱ ጊዜ መፍጀት ነው;;ጃዋርም በአሽሙር የተናገረውንም ማቅረብ ይቻላል::በእነዚህ ሽምጥ ጋላቢዎች ላይ ብዙ መናገር ይቻላል::የመልዕክቴ ነጥብ ግን ያ ! አይደለም::
ፖለቲከኞች ስግብግቦችና ራስ ወዳዶች ናቸው::በተለይ ሚዲያ ካገኙ  የሚናገሩትን አያውቁም::ልደቱ አያሌው  ፖለቲከኛ መሆን ከጀመረበት አንስቶ እስከ OMN ያለውን ቃለ መጠይቅ Perspective ፈፅሞ ረስቶታል ወይም ሥልጣን ከመመኘት ራዕዩ አኳያ ሲታይ “ደንዝዟል” ብል ትክክልኛ አቀራረብ ነው ::
ችግሩ የኢትዮዽያ ሚዲያ ዜና ወይም ታሪክ እመራረጥ ነው;;ባጭሩ ሚዲያዎች  ለአገር; ለሕዝብና  ለመጪው ትውልድ ከመጨነቅ ይልቅ  ለዕለቱ ላይክ;ሼርና ሰብስክራቭ ሲጨናነቁ ተስተውሏል::
በጣም  ጥቂቶችን ከፍ አናድርጋቸው::ባለ ራዕዮችን ከፍ እናድርጋቸው::Jዋርና ልደቱ  እንደ ኮረና ተጠቂዎቾና ሟቾች  ለማገንን የምትሞክሩትን ያህል ;
ኢትዮዽያ በማንኛውም ቅፅበት ተሯርጠው ከተጠቃሽ አንድ ፍሬ ጥሬዎች የበለጡ ፈጥኖ ደራሾች አሏት!
… ይሁንና አሁን ደግሞ የጃዋር ሲገርመን የልደቱ አዲስ ትርክት የኢትዮዽያ መፃኢ በማጨለም ተጀምሯል::በፖለቲካው አቋም ረገድ ጃዋርና ልደቱ ማዶ ለማዶ ናቸው::ስልጣንን በአቋራጭ ለመያዝና ሕዝብን ለማንሳሳት በዕኩይ የሴራ ፖለቲካ በአንድ ላይ መሰለፍ አማራጭ የሌለው ጋብቻ እንደሆነ አምነውበት ወደ አደባባይ ዉጥተዋል::እዚህ ላይ ችግሩ ሚዲያዎች ሁኔታውን ( በተለይ ዩ ቲዩብ ) በማራገብ ሁለት ፍሬ የማይሞሉ እፍኝቶችን  በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ  ወሳኝ እንደሆኑ በማስመሰል ሁኔታውን ማጮሁ ተገቢ አልነበረም:መልካምና ለአገር ግንባታ ጠቃሚ  የሆኑ ታዋቂ ፖለቲከኞች ; አክቲቪስቶችና የማሕበራዊ ሚዲያ  አቀንቃኞችን ድምፅ ማጉላት ለሁለንተናዊ  ዕድጉትና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት  አስተዋፅኦቸው በአረንጏዴ ቀለም መሠመር አለበት::
እንደኔ የኮረና ቫይረስ አዲስ ተጠቂና ሟች እየተለየ የሚጮህለትን ያህል ከህመሙ የተፈወሱና ቫይረሱን ለማጥፋት ፊት ለፊት የገጠሙ የህክምና ሳይንቲስቶች;ዶክተሮችና ነርሶች ገድል እምብዛምብ አይፃፍም ወይም አይወሳም::በኢትዮዽያ ሚዲያዎች የሚስተዋለው ነጭ ሃቅ ይኸው ነው ::
ኢትዮዽያ በአሁኑ ሰዓት አሁን ያለውን የአገራቱን ፖለቲካና ህገ መንግስት የሚተነትኑ  በርካታ  ፖለቲከኞችና ተንታኞች አሏት::ዕድሉ ሊሰጣቸው ይገባል!
ለሁለት ፍሬ ሥልጣን ናፋቂዎች ያን ያህል መንጫጫት ተገቢነቱ አይታየኝም::ኢትዮዽያ ትልቅ አገር ናት::
የኢትዮዽያ ሕዝብ ያለ;የሚኖርና የሚቀጥል ታሪክ ያለው ሕዝብ ነው::ከመስከረም ሰላሳ በኃላም ጥቅምት አንድ ነው::
ለሀገር በጎ ራዕይ ያላቸው ድምፃቸው ይሰማ !
Filed in: Amharic