>
5:13 pm - Tuesday April 19, 2608

ለወገኖቼ! (ጌታቸው አበራ)

ለወገኖቼ!

ጌታቸው አበራ


     …ነገደ ኩሽ  ወ  ሴም፣ ..’ኦሞቲክ፣ ናይሎቲክ’ …

  የእግዚአብሔር ፍጡራን፣

    የሰው ልጅ ዘር ግኝት ጥቁር ኢትዮጵያውያን..፤ 

    አያት ቅድመ-አያቶች፣.. ጥንተ-ኢትዮጵያ ልጆች.. 

       በገነቧት ሀገር፣ ሜዳ..ሸንተረሩ፣

    ከሰሜን .. እስከ ደቡብ፣ ከምዕራብ ወ  ምስራቅ.. በሰላም ስትኖሩ፤

    ያለ ስማችሁ ስም፣ ያለ ግብራችሁ ግብር.. ‘ቅጽል’ ተሰጥቷችሁ፣

    በአረመኔዎች እጅ፣ በጨካኞች በትር፣ በግፍ ያለፋችሁ፣ 

    በዘላለም ሕይወት መንግስተ-ሰማያት ይሁን ማረፊያችሁ!

  ••••••  

* በግፍ ለተገደለው ድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ እና በአገራቸው ምድር ላይ በሰላም ሲኖሩ፣ ምንም በማያውቁት ጉዳይ በአረመኔዎች እጅ በጭካኔያዊ አገዳደል ውድ ህይወታቸውን ላጡ ንጹሃን ዜጎች፣ የኢትዮጵያ ልጆች ሁሉ መታሰቢያ ትሁን!

* ሕይወታቸው ተርፎ በከባድ የአካል ጉዳት የሚሰቃዩ፣ ቤት ንብረታቸው ወድሞ መጠለያ በማጣት በየሜዳው የተበተኑ…፣በወገኖቻቸው ላይ በደረሰው አሰቃቂ ጭካኔያዊ ድርጊት ውዶቻቸውን ላጡና የሰው ልጅ አእምሮ ሊሸከመው በማይችል የህሊና መታወክ ውስጥ ላሉ፣ የእግዚአብሔር ቸርነትና ጥበቃ አይለያቸው፤ ጽናቱን ያጎናጽፍልን።

* ህሊና ያለን የዚያች ሀገር ሰዎች ሆይ! ይህን በወገኖቻችን ላይ የደረሰ፣ ለመስማትና ለማየት የሚዘገንን ጭካኔና ግፍ… ከዳር እስከዳር በማውገዝ፣ የዚህ አይነቱ ጸያፍና አሳፋሪ ከንቱ ድርጊት ዳግም በምድሪቱ ላይ ስፍራ እንዳይኖረው የበኩላችንን አስተዋጽኦ ከማበርከት ባሻገር፣ በጭንቀትና በችግር ላይ ለሚገኙ ወግኖቻችን እንድረስ!

Filed in: Amharic