>

ወላይቶች በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ማቅረባቸው ሊያስደንቃቸው እንጅ ሊያሳስራቸውም አይገባም!!! (መስከረም አበራ)

 ወላይቶች በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ማቅረባቸው ሊያስደንቃቸው እንጅ ሊያሳስራቸውም አይገባም!!!

መስከረም አበራ
 
የወላይታ የክልልነት ጥያቄ የሚያነሱ ፖለቲከኞች፣ምሁራን ትግላቸውን ሲጀምሩ ከመታገያ መርሆቻቸው አንዱ ከየትም ቦታ መጥቶ በወላይታ የሚኖር በማንኛውም የሰው ልጅ ላይ ምንም አይነት የግድያ ቀርቶ ግልምጫ እንዳይደረግ  የሚል ነበር።
 ወላይቶች ጨዋ ታጋዮች ናቸው።አንድም ሰው ገድለው፣በማንም ንብረት ላይ እጃቸውን አንስተው አያውቁም። የክልል ጥያቄ ያነሱትም ለፍተው ባቀኑት የአዋሳ ከተማ ጨምሮ በየሄዱበት መገደል ቢመራቸው ነው።
 የክልል እንሁን ጥያቄያቸው ከሲዳማ ጥያቄ የሚለይበት ነገር የለም። ጥያቄያቸውን ደም ሳያፈሱ ማቅረባቸው ሊያስደንቃቸው እንጅ ሊያሳስራቸውም ሊያስገድላቸው አይገባም።
 የክልል እንሁን ጥያቄ ተከትሎ በትላንትናው እለት በዞኑ ዋና ከተማ የተቀሰቀሰው ውጥረት ወደ አላስፈላጊ ግጭት ከማምራቱ በፊት መንግስት ጥንቃቄ በተሞላው መልኩ ችግሩን በውይይት እንዲፈታ ማድረግ አለበት። ከስፍራው በደረሰኝ መረጃ በትላንትናው ዕለት የነበረው የዞኑ አመራሮች ከተለያዩ አካላት ጋር በወይይት ላይ በነበሩት በውቅት በክልሉ ልዩ ሀይልና ፖሊስ ታፍነዉ መወሰዳቸውን ተከትሎ የተከሰተ ግጭት እና የመሳሪያ ተኩስም ነበር። ቁጥራቸው ወደ ሠላሳ የሚጠጋ ሰዎች በክልሉ ታጣቂዎች ታፍነው የታሰሩበት ለጊዜው እንደማይታወቅ የታሳሪዎች ቤተሰቦች አቤቱታቸውን እያሰሙ ነው። ትላንት በአካባቢው ነዋሪዎች እና በመከላከያ ሠራዊት መካከል በተፈጠረው ግጭትም ከሠራዊቱ በተተኮሰ ጥይት ተስፋዮ የተባለ ወጣት ሕይወቱ ማለፉ ታውቋል። በሲዳማ የተከሰተውን አይነት አላስፈላጊ ግጭት ለማስቀረት እድሉ ስላለ መንግስት ጉዳዩን በጥንቃቄ ሊይዘው ይገባል።
መንግስት እየመረጠ መግደሉን ያቁም  !!
 
ኦሮሚያ ላይ ይህንን ያክል ሰው ሲያልቅ፣ ሲዘረፍ፣ ሻሸመኔን የሚያክል ከተማ በቁሙ ሲነድ ሰላምን ለማስከበር ወላይታ ላይ ያደረገውን ግማሹን እንኳን ቢያደርግ ቢያንስ ከሞተው ግማሹ ሰው በተረፈ ነበር።
Filed in: Amharic