>

ሰው በቀስት ሆዱን ተመቶ አንጀቱ ተጎልጉሎ እዲወጣ የተደረገበት በአለም ላይ ከመተከል ውጭ  አልታየም አልተሰማም...!!! (ኮሚሽነር አበረ አዳሙ)

ሰው በቀስት ሆዱን ተመቶ አንጀቱ ተጎልጉሎ እዲወጣ የተደረገበት በአለም ላይ ከመተከል ውጭ  አልታየም አልተሰማም…!!!
ኮሚሽነር አበረ አዳሙ

“የፌደራል መንግስት ወይ ሀላፊነቱን ይወጣ አልያም ግዳጁን ለኛ ይስጠን”
ልዩ ኃይላችን የአማራ ልዩ ኃይል ተባለ እንጅ የኢትዮጵያ ልጅ (የኢትዮጵያ ሰራዊት)ነው፤
“ነፍሰጡር ሴት ሆዷ ተቀዶ ህፃኑ ወጦ የተበላበት፤
ሰው በቀስት ሆዱን ተመቶ አንጀቱ ተጎልጉሎ እዲወጣ የተደረገበት በአለም ላይ ከመተከል ውጭ የትም አልተፈፀመም፤
በትናንትናው እለት እንኳ 12 የመተከል አማራዎች እንደበግ ታርደዋል ይህን ፋሽስይች እንኳ አድርገውታል ብዬ ለማመን ይከብደኛል
ይሄን ድርጊት የፌዴራል መንግስት እንዲያስቆም ወይም ግዳጁን ለኛ እንዲሰጠን እየወተወትነ ነው።
ሀገር እንዳይፈርስ፣መጥፎ ታሪክ እንዳይሰራ በማሰብ እንዲሁም ጥቂቶች ባጠፉት ሁላችንም እንዳንሳሳት እንጅ የምንታገሰው ቤኒሻንጉል እየተፈፀመ ያለው ግፍ አይደለም መሳሪያ ሌላም ነገር እንድትጠቀም የሚያስገድድ ነው።
የአማራ ፖሊስ ኮሚሸን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ ከአማራ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ-መጠይቅ የተናገሩት።
ሙሉውን ቪዲዮ ለመመልከት ከስር ያለውን ሊንክ በመጫን ይከታተሉ
Filed in: Amharic