ክቡር ኮሚሽነሩ  ‹‹መንግሥት ያለ አይመስልም ነበር!›› የሚል ሪፖርት ቢያቀርቡም፣ እኔ ግን ‹‹አለን!›› እላለሁ…?!? (አሳዬ ድርቤ)

ክቡር ኮሚሽነሩ  ‹‹መንግሥት ያለ አይመስልም ነበር!›› የሚል ሪፖርት ቢያቀርቡም፣ እኔ ግን ‹‹አለን!›› እላለሁ…?!?

አሳዬ ድርቤ

 

ንጹሐንን የሚያስገድል! ኢንዱስትሪ የሚያወድም!
መንግሥትማ በጣም አለ፣ በአደባባይ የሚፎክር
በመንገድ ፈንታ መቃብር- በስካቫተር የሚያስቆፈር
ከፋፍሎ ያስገደለውን- አስተቃቅፎ የሚቀብር
የሠራው ወንጀል ሲጋለጥ- ቋንጣ ዜና የሚሰብር❗️
ኢትዮጵያማ መንግሥትማ አላት-
አገር አፍራሽ፣ ደም አፋሳሽ
ሤራ ጎንጉኖ ሲያበቃ- ፕሌን ተሳፍሮ የሚሸሽ፤
መንግሥትማ በጣም አለን- ያውም ባለ ብዙ ሃይል
ከሜንጫ ያመለጠን ሕዝብ- በጥይት ደረቱን የሚል
ነፍጠኛ የሚባል ሟች- ኦነግ ሸኔ ይሉት አራጅ
በአሳቡ ፈጥሮ ሲጨርስ- አማራን በጅምላ የሚፈጅ
በገሃድ ለቀጠፈው ነፍስ- ስውር ጦሩን የሚፈርጅ፡፡
መንግሥትማ በጣም አለን- የመኖር መብት ገፋፊ
ዛፍን ከምሣር ታድጎ- ሕፃን እና አራስ ጨፍጫፊ፡፡
መንግሥትማ በጣም አለን
አገር እንጂ የቸገረን…❗️

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.