>
5:13 pm - Saturday April 20, 9489

"ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ የትግሬ ሕዝብ መረዳት አለበት!" የሚለው ጥያቄ ከፍትሕና ከመርሕ አንጻር ሲፈተሽ!!! (ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

“ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ የትግሬ ሕዝብ መረዳት አለበት!” የሚለው ጥያቄ ከፍትሕና ከመርሕ አንጻር ሲፈተሽ!!!
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ባለፈው ሳምንት የኢትዮ 360ው ሀብታሙ አያሌው ከርዕዮት ሚዲያው ቴዎድሮስ ጸጋዬ ጋር አንድ ውይይት አድርገው ነበር፡፡ በወቅቱ ግን ከፌስቡክ ለአንድ ወር ታግጀ የነበርኩበት ጊዜ ስለነበር ስመለስ ይሄንን ለመጻፍ አስቤ ቀጠሮ በያዝኩት መሠረት ነው ይህችን መክተቤ፡፡
በዚያ ውይይት ላይ ቴዎድሮስ ጸጋዬ “ምሳሌ ልጥቀስና!” በማለት “የኦሮሞ ሕዝብ 90% የኦነግ ደጋፊ ቢሆን ይሄንን የኦሮሞ ሕዝብ ከዚህ የተሳሳተ አሰላለፉ እንዲወጣ መሥራት አለብን እንጅ ‘ኦነግ ሆኗልና መጥፋት አለበት!’ ማለት አለብን ወይ?” ብሎ በመጠየቅ “የትግራይ ሕዝብም በዚሁ አንጻር ታይቶ ‘ጥፋት አለበት!’ የሚባል ነገር ቢኖርም እንኳ ይቅርታ ተደርጎለት ሳይሆን ዜጋ ስለሆነ ብቻ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የኢትዮጵያ ሕዝብ የመደገፍ የመርዳት ግዴታ አለበት፡፡ ይሄ መሆን ካልቻለ የትግራይ ሕዝብ ከኢትዮጵያዊነቱ እንዲሸሽ ወይም እንዲገነጠል እየተገደደና እየተገፋ መሆኑን አጽንኦት ሰጥቸ መናገር እፈልጋለሁ!” በማለት ትንሽ እንኳ ሳያፍር ተናግሯል!!!
አየ ቴዎድሮስ ጸጋዬiii እስከዛሬ ድረስ ወያኔ ወይም የትግሬ ሕዝብ መገንጠል ፈልጎ ነገር ግን ኢትዮጵያዊነቱ ይዞት የተቀመጠ ይመስለዋል እንዴ??? ተገንጥሎ ምኑን ሊበላ ነው የሚገነጠለው??? ድንጋይ ሊበላ ነው??? የትግሬ ሕዝብ ከምግብ ጀምሮ እንደሀገር ለመቆም የሚያስችለው ሪሶርስ ቢኖረው ኖሮ ገና ድሮ በ1983ዓ.ም. ተገንጥሎ ነበር፡፡ ትግራይን ገንጥሎ እንደ ሀገር መኖር የሚያስችለው ሪሶርስና የዕለት ምግብ እንኳ እንደሌለው አውቆ ነው አርፎ የተቀመጠው!!! የመገንጠልን ካርድ ዐሥሬ የምትመዟት የኢትዮጵያን ሕዝብ በማስፈራራት ጥቅማቹህን ለማስጠበቅ ብቻ እንጅ በግድ “ተገንጠሉ!” ብለን ብንወጋቹህ እንኳ አታደርጉትምና ማስመሰሉ ይብቃቹህ!!!
ቴዎድሮስ ጸጋዬ”…የትግራይ ሕዝብ ‘ጥፋት አለበት!’ የሚባል ነገር ቢኖር እንኳ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መረዳት አለበት…!” ብሎ መርሕን የጣሰ ጥያቄ ሲያነሣ ሁለት ፈጽሞ ሊጠየቁ የማይገባቸውን ጥያቄዎች እየጠየቀን እንደሆነ ፈጽሞ ሊረዳ አልቻለም!!!
1ኛው. “የትግሬን ሕዝብ ከፍትሕ በላይ አድርጉት!” ብሎ መጠየቁ ሲሆን፡፡
2ኛው. ደግሞ የኢትዮጵያን ሕዝብ በተለይም አማራውን “ከእግዚአብሔር በላይ ይቅር ባይ፣ በደልን የማታስቡ፣ ፍጹም ታጋሽና ከባቴ አበሳ ሁኑ!” ብሎ መጠየቁ እንደሆነ ፈጽሞ ሊገባው አልቻለም!!!
ቴዎድሮስ ጸጋዬ “የዘመድ ቄስ እየፈታ ያለቅሳል!” እንዲሉ ጉዳዩ የዘመዶቹ ጉዳይ ሆኖበት የዚህን ያህል ፍጹም ወገንተኛና በእጅጉ ሚዛናዊነት የጎደለው እንዲሆን አስገድዶታል፡፡ ችግሩ የጠየቀውን ነገር ማድረግ ይቻላል ወይ? የሚለው ነው፡፡ ማለትም ሰው ከእግዚአብሔር በላይ ይቅር ባይ፣ በደልን የማያስብ፣ ፍጹም ታጋሽና ከባቴ አበሳ መሆን ይችላል ወይ??? ከእግዚአብሔር በላይ ስላቹህ የእግዚአብሔር ትዕግሥት፣ መቻል፣ ማሳለፍና አበሳ በደል ደባቂነት እንኳ ልክ አለውና ነው እንኳንና የሰው ልጅ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን ስታነቡ በብዙ ቦታዎች እንደምትረዱት ለምሳሌ እግዚአብሔር ከትዕግሥቱ፣ ከመቻሉና ከማሳለፉ በላይ የሆኑበትን የሰዶምና የጎሞራን ሰዎች እሳትን ከሰማይ አዝንቦ እንዳጠፋቸው ታውቃላቹህ ዘፍ. 19፤5-26 ፣ የኖኅ ዘመን ሰዎችንም እንደዚያው ዘፍ. 7፡፡ በርካታ የበደሉ ግለሰቦችንም እንደዚያው፡፡ ያውም እነዚህ የሰዶም ገሞራና የኖኅ ዘመን ሰዎች እግዚአብሔር “የእናንተ ነገር በቃኝ!” ብሎ ሊያጠፋቸው የቻለው “ዝሙትን አበዙ!” ተብሎ ነው፡፡ እንደ የትግሬ ሕዝብ በምድር ላይ አለ የተባለውን አረመኔያዊ ግፍ፣ በደልና አበሳ ሁሉ አጋንንትን እንኳ በሚያስንቅ ደረጃ የፈጸሙ አይደሉም!!!
እና ታዲያ እኛ ከእግዚአብሔር እንኳ በላይ ወይም የላቅን ሆነን፣ ፍትሕን ዋጋ አሳጥተንና መርሕን ቀብረን የትግሬ ሕዝብ ወያኔን ወልዶ አሳድጎና ልጆቹን ገብሮ  ውጫዊና ውስጣዊ መልካም አጋጣሚዎችን፣ ዕድሎችንና ምርኩዞችን በመጠቀም ለሥልጣን አብቅቶ የፈጸመብንን ወይም እንዲፈጸምብን ያደረገውን በርካታ ሚሊዮን ወገኖቻችን ያለቁበትን የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ፣ በቃላት ሊገለጽ የማይችል አረመኔያዊ ግፍና ሰቆቃን፣ መጠን የለሽ ዝርፊያንና ውንብድናን ወዘተርፈ. ለሠላሳና አርባ ዓመታት የፈጸመብንን ግፍ በደልና ሰቆቃ ጨርሶ ሳንመለከት ሳናስብና ሳንቆጥር የትግሬን ሕዝብ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ መርዳት መደገፍ ይቻለናል ወይ???
ሰው መሆናችን ከጣለብን ተፈጥሯዊ ገደብ ወጥተን ይሄንን ማሰብና ማድረግ ይቻለናል ወይ??? እሱ ቴዎድሮስ ጸጋዬስ የፈለገውን ያህል ወገናዊነት ቢያጠቃው እንኳ እንዴት ያለ ማየት፣ ማሰብ፣ ማመዛዘን የተሳነው ቢሆን ነው እንዲህ ዓይነት ፈጽሞ የማይቻል ጥያቄ ሊጠይቀን የቻለው??? ሰው በሚዛናዊነት ስም ቀርቦ የዚህን ያህል ከሚዛናዊነት እጅግ በመራቅ ጭፍን ወገናዊና አድሏዊ መሆን እንደሚችል ደንበኛ ማሳያ ነው ቴዎድሮስ ጸጋዬ ማለት!!!
በእርግጥ የአንድነት ኃይል ሥልጣን ላይ ቢሆን ኖሮ ቴዎድሮስ ጸጋዬ እንዳለው ወያኔን የፈጠረውንና “ጃዝ!” እያለ ሲያስፈጀንና ሲያዘርፈን የኖረውን ወያኔውን የትግሬን ሕዝብ እና ከኦሮሞ ሕዝብ ደግሞ ኦነግ የሆነውን ከጥፋት አሰላለፋቸው አውጥቶ ወደ መሀል ለማምጣት ከወያኔና ኦነግ ጋር ከማጥፋት ውጭ የሆነ አማራጭ መጠቀም ተገቢ በሆነ ነበር፡፡ አሁን ግን ኃይልና ሥልጣን በእነዚህ የጥፋት ኃይሎችና አውሬዎች እጅ በሆነበት ሁኔታ የአንድነት ኃይሉ እንዲህ አስቦ ቢቀጥል ተቀረጣጥፎ ከመበላትና ከማለቅ ውጭ ሌላ ዕድል አይኖረውም!!!
ትግላችን የህልውና ትግል የsurvival በሆነበት ሁኔታ እያንዳንዷ በከንቱ የምናባክናት ደቂቃ ከአንድነት ኃይሉ ወይም ከወገኖቻችን በርካቶች እየተበሉ እንደቅጠል እየረገፉ ባሉበት ሁኔታ አንዲትም እንኳ በከንቱ የሚያባክነው ጊዜ ሳይኖረው ሕልውናውን ለመታደግ ቆርጦ መፋለም አለበት እንጅ መቸ እንዲህ “አስተምረን እንመልሳለን!” ብሎ ለሚዘባነንበት የድሎት ጊዜ ላይ ሆነና ነው እንዲህ ሊያስብ የሚገባው ወይም የሚገደደው???
ግርም የሚለኝ ነገር “ወያኔና የትግሬ ሕዝብ አንድ አይደሉም!” የሚሉ ሰዎች ይሄንን የሚሉን አንድ አለመሆናቸውን ልክ መሬት ላይ ወርደው ጥናት አድርገው ያረጋገጡ መስለው መናገራቸው ነው፡፡ ትግራይን እረግጦ የማያውቀው ሁሉ እየተነሣ “ወያኔና የትግሬ ሕዝብ አንድ አይደሉም!” ይላል፡፡ እኔ ግን ወያኔና የትግሬ ሕዝብ ፍጹም አንድ መሆናቸውን፣ ወያኔን እንዲህ አድርጎ አክፍቶ የፈጠረው የትግሬ ሕዝብ መሆኑን በአንድ ቀላል ምሳሌ ላረጋግጥላቹህ እችላለሁ!!!
እሱም ምን መሰላቹህ ማንኛውም ትግሬ ከሕፃን እስከ ሽማግሌ ወያኔ በሕገወጥ መንገድ ያለ ነዋሪው ፈቃድና ይሁንታ እንዲሁም ያለ ታሪካዊ ዳራው ከጎንደርና ከወሎ ቆርሶ ወስዶት ስለነበረው የአማራ መሬት ብትጠይቁት ወደ አማራ እንዲመለስ አይፈልግም፡፡ “ለአማራ መመለስ አለበት!” የሚላቹህ አንድ ትግሬ አታገኙም፡፡ ይሄ ብቻ ሳይሆን ወያኔ ከኢትዮጵያ ዘርፎ የወሰደውን በብዙ ቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር ሀብትንና የተለያየ ዓይነት ንብረትንም እንደዚያው!!! ሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እየሞተ ወያኔን ሲቃወምና ሲታገል የትግሬ ሕዝብ ለአንድ ቀን እንኳ ወያኔን ሲቃወም አይታቹህት ታውቃላቹህ???
ከትግሬ ሕዝብ እንደ አረና፣ ባይቶና፣ ሣልሳይ ወያኔ ምንንትስ ምንንትስ የተባሉ ተቃዋሚ ድርጅቶች ወጡ ቢባል እንኳ ከወያኔ የባሰ ወያኔ ለመሆን የሚያስቡ ሆኑ እንጅ ወያኔ የፈጸማቸውን ግፍ፣ ዝርፊያና ውንብድ አርሞ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በእኩልነት ለመኖር የሚያስብ የተቃውሞ ፓርቲ ከትግሬ ሕዝብ ወጥቶ አያውቅም ወደፊትም አይወጣም!!!
አሉ ደሞ ሌሎች “በወያኔ አገዛዝ የወያኔ ባለሥልጣናትና ቤተሰቦቻቸው ተጠቀሙ እንጅ የትግራይ ሕዝብ አልተጠቀመም!” የሚሉ ደናቁርት፡፡ ይሄም በጥናት ላይ የተመሠረተ ቢሆን ባልከፋ ነበር፡፡ አንድ ቀላል ምሳሌ ልስጣቹህ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዘገባ መሠረት በመሠረተ ልማት መሟላት (በመንገድ፣ በውኃ፣ በመብራት፣ በጤናና በትምህርት ተቋማት መሟላት) ኢትዮጵያ ውስጥ ክልሎች ከሚሏቸው ትግራይ አንደኛ ናት፡፡ ወያኔ ይሄንን ማድረግ የቻለው በዝርፊያና ኢፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖር በማድረግ ነው!!!
ደናቁርቱ ግን ወያኔ ሆን ብሎ ለማጭበርበር እንዲመቸው ችግሩን እንዳይፈታ አድርጎ ያቆየውን የመቀሌን የውኃ ችግር እየጠቀሱ ከዚህ በላይ ወያኔ ለትግራይ የሠራውን የኢንደስትሪ መዓትና መሠረተ ልማት ይረሳና “ሌላው ቀርቶ ለዋና ከተማቸው ለመቀሌ እንኳ የውኃ ችግራቸውን ያልፈቱ ሰዎች ናቸው!” ይላል!!! አይገርምም???
“ትግራይ በመሠረተ ልማት ከኢትዮጵያ አንደኛ ናት!” ማለት በወያኔ ዝርፊያ የትግራይ ሕዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የበለጠ ተጠቃሚ ሆነ ማለት አይደለም ወይ??? ወያኔ እያንዳንዱን ትግሬ ሚሊየነር አድርጎት ስታዩ ነው ወይ በወያኔ ዝርፊያ የትግራይ ሕዝብ ተለይቶ መጠቀሙ የሚገባቹህ??? ምንም እንኳ የወያኔ ሕልም ይሄንን ማድረግ ቢሆንም ይሄንን ለማድረግ ግን የሀገሪቱ አቅምስ ይፈቅድላቸዋል ወይ እነ ደናቁርት???
እናም ወያኔን ወያኔ ያደረገው ወይም ዘራፊና ወንበዴ እንዲሆን ያደረገው የትግሬ ሕዝብ ነው፡፡ ወያኔ ማለት ዘራፊ፣ ቀማኛ፣ ወንበዴ ማለት ነው፡፡ ወያኔ የሚለው ቃል አሁን ወያኔ ሲመጣ አዲስ የተፈጠረ ቃል አይደለም፡፡ በቋንቋቸው ውስጥ የኖረና ወያኔነትን እንደጀግንነት የሚቆጥር ማኅበረሰብ ነው የትግሬ ሕዝብ ማለት!!!
እናም የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በከንቱ ተስፋ የማይደረግ ነገር ተስፋ አድርገህ ውድ ጊዜህን አታባክን፡፡ በከንቱ የምታባክናት እያንዳንዷ ዕለት ይዛህ መቀመቅ እየወረደች መሆኗን ዕወቅና ተነሥ!!!
Filed in: Amharic