![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2021/03/FB_IMG_1614851725205-300x272.jpg)
“…ሀገር ስታምጥ!” የሁላችንም ታሪክ ነው ብታነቡት ታተርፋላችሁ….!!!”
![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2021/03/FB_IMG_1614851725205-300x272.jpg)
እስክንድር ከቃሊቲ
ቀለብ ስዩምን ለማወቅ የቻልኩት የኢትዮጵያ ህዝብ ግንቦሩን ለጥይት በመሰጠት ገ ዢዎቻችን ሳይወዱ በግዱ 2010 ዓ.ም ከእስር ቤት እንዲለቁን ካስገደዳቸው በኃላ ነበር ። ያሳለፍነው የእስር ዘመን በእጅጉ አድካሚ የነበር በመሆኑም ብዙዎች ከእኛ በላይ መሰዋት የሆነለት ዲሞክራሲ እና![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2021/03/FB_IMG_1614851722458-173x300.jpg)
ከእስር መለቀቅ እውን አለመሆኑ ቀጣይ ትግል እንደሚጠይቅ በመተማመን ጊዜ አልፈጀብንም በዛ መንግድ ተጉዘንም ይሄው አሁንም ቃሊቲ እስር ቤት እንገኛለን ።
![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2021/03/FB_IMG_1614851722458-173x300.jpg)
ይህች ኢትዮጵያዊት ጀግና ሴት በዚህ እስር ቤት ሁና የፃፈችውን ይህን መፅሐፍ ለማንበብ ዕድሉን ባላገኝም መነበብ የሚገባው መፅሐፍ መሆኑን አልጠራጠርም ። የእሷ ታሪክ የህዝብ ታሪክ ክፋይ ነውና ። የዚችን ዕልፈት ጀግኒት ታሪክ እንድታነቡት በታላቅ ትህትና የምጋብዛችሁ ብዙ ቁምነገር እንድምታገኙበት በመተማመን ነው ።
የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ፕሬዝዳንት
እስክንድር ነጋ
( ከቃሊቲ እስር ቤት)