>
5:13 pm - Wednesday April 19, 0626

ነገረ ኦሮሙማ....!!!   (ዘመድኩን በቀለ)

ነገረ ኦሮሙማ….!!!  

ዘመድኩን በቀለ

 
በትናንትናው የዐማሮች ሰልፍ ላይ ከታዩት አስደማሚ የሰውነት ከፍታ፣ የሥልጣኔን ጥግ መድረስን ከሚያሳየው አስተማሪ ሰልፍ ውስጥ አንዲት በወልድያ የታየች መፈክር መዘው በማውጣት አራጅ አሳራጁ ነፍሰ በላው ቡድን ሲንጫጫ ውሎ አድሯል። ” ኦሮሙማ ይውደም፣ ኢትዮጵያ ትቅደም ” ይሄ ቀል ነው ያንጫጫቸው። 
 
… በዚህ ቃል የተነሣ ኦነጉ የኦሮሙማ አቀንቃኝና መሪ ኦቦ ታዬ ደንደአ የዐማራ ነገድ ላይ የሩዋንዳው ዓይነት የዘር ጭፍጨፋ እንዲካሄድ በውስጠዝ አዟል። https://www.facebook.com/312860729331033/posts/833485423935225/ 
 
… ያ የበግ ለምድ የለበሰው ተኩላው አፍቃሬ ኦነግ፣ ዐማሮቹን ከሚስቱ ጋር ተመካክሮ በኢትዮጵያ ስም ጎፈንድሚ ሲሸቅልባቸው የከረመው መስፍን ፈይሳማ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ” በአደባባይ በመቅደድ የኦሮሙማ ሃይማኖት ተከታይ መሆኑን በይፋ አረጋግጧል። 
 
 
አዎ እርግጥ ነው የኦሮሙማ ቀጥተኛ ትርጉሙ ኦሮሞነት ማለት ነው። ይሄ የቃሉ ትርጉም ነው። ልክ ዐማሩማ ሲባልም ዐማራነት፣ ጉራጉማ ጉራጌነት፣ ሶማሉማ ሶማሌነት ወዘተ እንዲሉ ማለት ነው። ይሄ መደበኛና ቀጥተኛ ተራ ቀላል ትርጉሙ ነው። በዚህ ላይ ዶ/ር ደረጄም ማብራሪያ ሰጥቷል። የደበቀው ግን ዋነኛውን የኦሮሙማ ትርጉም ነው። ወርቁን ደብቆ በሰሙ መንጫጫት ፋርነት ነው። ሞኝህን ፈልግ። 
 
… የእነ ዐቢይ አሕመድ፣ የእነ ታዬ ደንደአ፣ የእነ ሽመልስ አብዲሳ ኦሮሙማ ትርጉም ግን እንደ ላይኛው ዓይነት ትርጉም ያለው አይደለም። ራሱን የቻለ የሃይማኖት ትርጉም ነው የሚሰጡት። በእነሱ የመዝገበ ቃላት ፍቺ ኦሮሙማው ሃይማኖት ነው። ኦሮሙማው ክርስቲያን ኦሮሞንም ሙስሊም ኦሮሞንም በኦሮሞነት አይቀበልም። ኦሮሙማን የሚያገኘው እስላም ኦሮሞም ሆነ ክርስቲያን ኦሮሞ የኦሮሙማን የዋቄፈታ ሃይማኖት የተቀበለ እንደሆነ ብቻ ነው። 
 
የዚህ ነገር ፍቺና ምስጢር እንዲገባችሁ ይሄንን የአቻሜለሁ ታምሩን ጦማር ማንበቡ ጠቃሚ ነው። 
 
… ይሄኛው የእነ ዐቢይ ኦሮሙማ ተስፋፊ ነው። ይሄኛው ኦሮሙማ ሰልቃጭ ነው። ይሄኛው ኦሮሙማ አውዳሚ ነው። ከተሞች ያጠፋል። ኦሮሙማን ያልተቀበሉ ኦሮሞ ያልሆኑ ነገዶችን በሙሉ ያርዳል ያጠፋል። ህጻን፣ ወንድ ሴት እርጉዝ ሳይል ይጨፈጭፋል። አብያተ ክርስቲያናትን በሙሉ ያወድማል። ይሄኛው ኦሮሙማ ያ የዋቄፈታው ኦሮሙማ ነው። በቃኝ አያውቅም። አክሱም፣ መቀሌ፣ አዲግራት የኔ ነው፣ ጎንደር፣ ጎጃም ወሎ የእኔ ነው። ሲዳማ፣ ሶማሌ፣ አፋር የእኔ ነው። ሀረሬ፣ ድሬደዋ የእኔ ነው። በቃ የእኔ ነው ባይ ነው የእነ ዐቢይ አሕመድ ኦሮሙማ። 
 
… ትናንት ዐማሮቹ የተቃወሙት ይሄኛውን ኦሮሙማ ነው። የሉባው ዐቢይ አሕመድን የወራሪው አባ ገዳይ ዐቢይ አሕመድን ኦሮሙማ ነው የተቃወሙት። ኦሮሞነትን ሳይሆን ኦሮሙማ ወራሪነትን፣ ኦሮሙማ ገዳይነትን፣ እሱን ነው የተቃወሙት። ዛሬም ተቃውሞው ቀጥሏል። ነገም ይቀጥላል። ላለመስልቀጥ፣ ላለመታረድ፣ ላለመውደም ሲባል ተቃውሞው ይቀጥላል። ዛሬ ዐማራው፣ ነገ ሲዳማው፣ ደቡብ በሙሉ ሰልቃጩን ኦሮሙማ ይቃወማል። 
 
… አዲስ አበባም የገጠማት ይሄኛው ኦሮሙማ ነው። ዋጥ ስልቅጥ የሚያደርገው የዋቄፈታው ኦሮሙማ። ይሄኛው ኦሮሙማ ልክ እንደ ትግራዋይ እንደሚሉት አይነት ሃይማኖት ነው። ሁሉን መጠቅለል። ባንኩንም፣ ታንኩንም መጠቅለል። መውሰድ። ሁለቱም ፀረ ታሪክ ናቸው። ቅርስ ማውደም። ማበላሸት፣ ታሪክ ማጥፋት ናቸው። ታከለ ኡማም፣ አዳነች አቤቤም በአዲስ አበባ ታሪካዊ ሥፍራዎችን የሚያጠፉት፣ የሚያቃጥሉት፣ የሚያወድሙት፣ በዶዘር፣ በኤክስባታር የሚንዱት ኦሮሙማ ሃይማኖት ሌላ ታሪክ ስለማይፈልግ ነው። 
 
… በዚህ በኦሮሙማ ሃይማኖት እነ አሩሲ፣ ወለጋ፣ ሸዋ ቀደም ሲል ተውጠዋል። ኦሮሙማ ሃይማኖትን በግድ ተቀብለው ኦሮሞ ነኝ እንዲሉ ተደርገዋል። ዛሬ በወለጋ ዐማሮችን የሚያጸዳው ያ ኦሮሙማ ፕሮጀክት ነው። ቤኒሻንጉል ገብቶ የሚያጸዳው ኦሮሙማ ፕሮጀክት ነው። ሰሜን ሸዋን እያጸዳ የሚገኘው ኦሮሙማ ሃይማኖት ነው። የኦሮሙማ ሃይማኖት ኦሮሞ እስላሞችን ለዚህ ፕሮጀክት ክርስቲያኖችን እንዲያጸዱለት ይጠቀምባቸዋል። ዋቄፈታዎቹ ደግሞ ኦርቶዶክሱንና ኦሮሞና እስላም ዐማሮቹን ያርዱለታል። ፕሮቴስታንቱ ኦሮሞ ስንቅና ትጥቅ አቅራቢ ነው። በሰበካም የኦሮሙማን የካድሬነትን ሥራ በህዝቡ ለማስረጽ ይሠራላቸዋል። ጴንጤ ያስገድላል እንጂ አይገድልም የሚለው አባባል ድሮ ቀረ የሚሉም አሉ። መጨረሻ ላይ ግን ሁለቱም ጴንጤውም፣ እስላሙም ኦሮሞ የኦሮሙማን የዋቄፈታ ሃይማኖት መቀበል የግድ ይላቸዋል። ዋቄፈታን ሳይቀበሉ ኦሮሙማነት የለም። 
 
… እውነታው ይሄ ነው። ዛሬ ዐማራ ሲገደል፣ ሲጨፈጨፍ፣ ሲወድም፣ ሲሰደድ፣ ሲያለቅስ፣ ሲፈናቀል፣ ሲታረድ ቆመህ ያየህ፣ ዝም ያልክ በሙሉ ሩቅ ሳይሆን በቅርቡ ጠብቅ። ሲዳማን ሲወሯት ጠብቅ። ደቡብ በጉጂ በኩል፣ በነጭ ሳር ወደ አርባምንጭ ጠብቅ። ጠብቅ ደቡብ ኢትዮጵያን ጠብቅ። በአፋር፣ በሶማሌ፣ በቤኒሻንጉል ጠብቅ። ከዐማራ ጋር ተሰልፈህ ትሄን ሰልቃጭ ኦሮሙማ የተባለ ሃይማኖት በጊዜ መግታት ካልቻልክ ለሁሉም የማትሆን ኢትዮጵያን በቅርቡ እናያለን ማለት ነው። እነ ዐቢይ አሕመድ፣ እነ ሽመልስ አብዲሳ፣ እነ ብርሃኑ ጁላ በሰሜን ሸዋ ያስታጠቁት አቢይሸኔ ቡድን ዛሬ ራሱ በደቡብ ኢትዮጵያ ሥራውን ጀምሯል። 
 
 
… በሎንዶኑ ስብሰባ ጃዋርም ሆነ ሌሎቹም የኦሮሞ ሙሑራን ያሉቱ ይሄንኑ ነው። ” ለእኛ የማትመች ኢትዮጵያን ብትንትኗን ነው የምናወጣው” ይሄው ነው እየሆነ ያለው። አሁን ትግሬ ወድሟል። ዐማራ እየወደመ ነው። ደቡብ ተጀምሯል። አፋርና ሱማሌን እያባሉ ነው። ምዕራብ ኢትዮጵያ ወድሟል። መተከል ወድሟል። አዲስ አበባ ዳርዳሯ ወድማ መሃሏ ስጋት ላይ ነው። ባሌ፣ አሩሲ፣ ሻሸመኔ፣ ጅማ ዐማራና ኦርቶዶክሱ ወድሟል። ሰሜን ሸዋ ወድሟል። የአጣዬን ከተማ በአንድ ቀን ወደ ዐመድነት የለወጡት። የእነ ዐቢይ አሕመድ ኦሮሙማ ማለት ይሄ ነው። ወራሪነት፣ አውዳሚነት፣ ዘር አጥፊነት ነው የእነ ዐቢይ አሕመድ ኦሮሙማ። እንጂ በቀጥተኛ ትርጉሙ ኦሮሞ የሚለውን ቃል አይደለም የእነ አቢይ ኦሮሙማ።  
 
… ኦሮሙማ ሃይማኖት በካርታ ተሠርቶ፣ ከሱዳን ድንበር ተጋርቶ፣ ሰሜን ሸዋንና ሰሜን ወሎን ጠቅልሎ፣ ከትግራይ ተጎራብቶ፣ ከጎጃም ከቤኒሻንጉል ወስዶ በሥራ ላይ ነው ያለው። 
 
… ይልቅ የጨዋውን ዐማራ ህዝብ ጥያቄ ወደ አንድ በቦታው ላይ ወደሌለ የፖለቲካ ፓርቲ አዙራችሁ አጀንዳ ለማስቀየስ ከምትንበጫበጩ የዐማራ ህዝብ ለጠየቃችሁ ጥያቄ ምላሻችሁን ቁጭ አድርጉ። ዐማራን ከኦሮሚያ አጽድተህ እጨርሳለሁ ማለት አሳን ከውቅያኖስ አጥምጄ እጨርሳለሁ እንደማለት ነው። አትግደለኝ ለሚልህ ህዝብ እንደፈሪ ከቆጠርከው አንተ የታጠቅከውን ሱሪ እሱም እንደታጠቀው ማወቅ አለብህ። ዝም ብሎ እየታረደ ከማለቁ በፊት የወንድ ሞት ሞቶ ቢሞት አይቆጭም። አጣዬ ላይ የአንድ ሆቴል ባለቤት የሆኑ የዐማራ አዛውንት ” የእነ ዐቢይ፣ ታዬ ደንደአ ኦሮሙማ የ13 የ14 ዓመት ህጻናትን እንዲያርዷቸው በማደር ነው የኦሮሙማን መንፈስ ሲያጠምቋቸው የነበረው። እናም ዐማራ ያለው አንድ ዐማራጭ ብቻ ነው። ላለመሞት መሞት። አከተመ። 
 
ከኑመጋ ዱቢን  !!
Filed in: Amharic