>

የአማራ ሕዝብ ፍጅት የሀገራችን ቁጥር አንድ የብሔራዊ ደኅንንት ስጋት ነው! (የህግ ጠበቃ እና የህግ ምሁር  መላኩ ሹምዬ)

የአማራ ሕዝብ ፍጅት የሀገራችን ቁጥር አንድ የብሔራዊ ደኅንንት ስጋት ነው!

የህግ ጠበቃ እና የህግ ምሁር  መላኩ ሹምዬ

የሕዝብ እልቂትና መፈናቀል በአጠቃላይ: በተለይም በአማራ ሕዝብ ላይ የቀጠለው መጠነ ሰፊ እልቂት እና መፈናቀል የሀገራችን ቁጥር አንድ የብሔራዊ ደኅንነት ችግር ተደርጎ መወሰድ አለበት::
ለችግሩ የሚመጥን አፋጣኝ እና ፍቱን የፖለቲካና ፀጥታ እርምጃ በመውሰድ እልቂቱን ማስቆም የሁላችንም: የሀገርንም ኅልውና የማረጋገጥ ጉዳይ መሆኑ ለአፍታም ቢሆን መረሳት የለበትም:: በተለይ ሥልጣን ላይ ያላችሁ አካላት ለሕዝቡና ሀገር ብላችሁ ባይሆን እንኳ ለራሳችሁ ስትሉ እልቂቱን አስቁሙ::
ሕዝቡም እየጠየቃችሁ ያለው መንግስት የተቋቋመበትን ቀዳሚ ዓላማ-የጋራ ደኅንንታችን አረጋግጡልን ብሎ ነው:: This is not by any means a tall order. በመንግሥት መዋቅር የሚደገፍ እልቂት ይቁም ነው ያለው:: በየትኛውም መለኪያ ጊዜ የሚሰጥ ወይም የቅንጦት ጥያቄ አይደለም:: ከዚህ ያንሰ ጥያቄም ያለ አይመስለኝም::
የሕዝብ እልቂት ማስቆም ካልቻላችሁ ሀገራችን የምትገባበት የደኅንንት ቃውስ ለማሰብም የሚዘገንን እንደሚሆን ለመረዳት የፖለቲካና ደኅንንት ጉዳዮች ሊቅ መሆንን አይጠይቅም::
Filed in: Amharic