>

በኢትዮጵያ ሠማይ ሥር እየተካሄዱ ላሉ አስር እውነቶች እጮሃለሁ!  (አሰፋ ሀይሉ)

በኢትዮጵያ ሠማይ ሥር እየተካሄዱ ላሉ አስር እውነቶች እጮሃለሁ!

 አሰፋ ሀይሉ

1. በኦነግ-መራሹ መንግሥት በትግራይ ህዝብ ላይ በትግራይ እየተካሄደ ያለው ጭፍጨፋ እንዲቆም እጮሃለሁ!
2. በኦነግ-መራሹ መንግሥት በአማራ ህዝብ እና በኦርቶዶክስ ክርስትያኖች ላይ በኦሮሚያና በጉሙዝ እየተካሄደ ያለው ጭፍጨፋ እንዲቆም እጮሃለሁ!
3. በኦነግ-መራሹ መንግሥት ሰብዓዊ መብታቸው ተረግጦ በእሥር የሚንገላቱት እነ እስክንድርና ሌሎች እንዲለቀቁ እጮሃለሁ!
4. በኦነግ-መራሹ መንግሥት የአማራ ሀይል ከራሱ ምድር (ከወልቃይት-ሑመራ-ፀለምት-ራያ) ለማስወጣት ‹‹አማራ ከምዕራብ ትግራይ ይውጣ›› በሚል ከኢዜማና ዓለማቀፍ ሀይሎች ጋር እየተዶለተ ያለው መጠነ-ሰፊ ሴራ በአስቸኳይ እንዲቆም እጮሃለሁ!
5. ኦነግ-መራሹ መንግሥት የተሳሳተ መረጃ ለዓለም በማሰራጨት እያደረገ ያለውን ፀረ-አማራ በጀርባ የማስወጋት ሴራ ለማክሸፍ፣ በቻልኩት ሁሉ መንገድ፣ የውጪ መንግሥታትና ዓለማቀፍ ተቋማት የአማራ ሕዝብ ወደታሪካዊ ግዛቱ እንደተመለሰ እንዲያውቁ አብክሬ እጮሃለሁ!
6. በኦነግ-መራሹ መንግሥት ግብዣ ወደ አልፋሽካ የገባው የሱዳን ጦር ሠራዊት ከኢትዮጵያ ምድር እንዲወጣ እጮሃለሁ!
7. በኦነግ-መራሹ መንግሥት ግብዣ እስከ አክሱምና አድዋ የገባው የኤርትራ ሕዝብ ሠራዊት ለአላስፈላጊ ጦስ ከመዳረጉ በፊት ከኢትዮጵያ ግዛት እንዲወጣ እጮሃለሁ!
8. በኦነግ-መራሹ መንግሥት እየተቀነባበሩ ያሉ ዘረኛ፣ ጠባብና ከፋፋይ የኦሮሙማ ፋሺስታዊ ሴራዎችና ፕሮጀክቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ከሁሉም ጉዳዮች በላይ አብዝቼ እጮሃለሁ!
9. በኦነግ-መራሹ መንግሥት አማካይነት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የተደቀነው ሥጋት ከወያኔም ሆነ ከማንኛውም ውጫዊ አካል ከሚመጣ ሥጋት ሁሉ የበለጠ የህልውና ሥጋት ውስጥ የሚጨምረን መሆኑን ደግሜ ደጋግሜ ሚሊዮን ጊዜ እጮሃለሁ!
10. በኦነግ-መራሹ መንግሥት የተጠለፈው የመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ፀረ-ኢህአዴግ የዲሞክራሲ ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል አምባገነኑና ገዳዩ ኢህአዴግ ከሥልጣን እስኪወርድና የተመኘነው ለውጥ እስኪመጣ ድረስ፣ ትንፋሼ እስከፈቀደልኝ ደጋግሜ እጮሃለሁ!
አንድ ቀን ጩኸታችን ወደ እውነተኛ ተጋድሎ ይቀየራል!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!
ይኸው ነው!
Filed in: Amharic