>
5:13 pm - Wednesday April 19, 8243

ኤርሚያስ ለገሰ ለ42ቱ ከእስር ለተለቀቁት እስረኞች 52 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል ....!!!

ኤርሚያስ ለገሰ ለ42ቱ ከእስር ለተለቀቁት እስረኞች 52 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል ….!!!
ባሻዬ ጭንቁ

 

• ቅኔው ልዩ እንደሆነ ለተነገረለት ምልዕክታዊ የእስረኞች ፍቺ ፤ 
        ከጅምላ አፈሳ ከእስር እንዲለቀቅ ለእያንዳንዳቸው የተጠየቀውን የ1ሺህ ብር የማስያዣ ዋስትና ፤ በአጠቃላይ
42 ሺህ ብር እና ተጨማሪ 10ሺህ ብር በድምሩ 52 ሺህ ብር አቶ ኤርምያስ ለገሰ Ermias Legesse Wakjira  ድጋፍ አድርጓል ።
    ከዚህ ቀደም እንደሚታወቀው ፤በመለስ ትሩፋት ባለቤት አልባ ከተማ መፅሀፍ ከተገኘ የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበር አቶ አንዱአለም አራጌ  ከመፅሓፉ ከተገኘው  ገቢ ሃያ በመቶው እሱ በእስር ቤት እያለ ለሁለት ልጆችህ የተወሰኑ ወራት የትምህርት ቤት ወጪ እንዲሆን 90 ሺህ ብር ድጋፍ ማድረጉ የሚታወቅ ነው።
     ከዚህም በተጨማሪ ፤የመለስ ልቃቂት በሚለው መፅሀፉ ደግሞ ከመፃሓፉ ሽያጭ ከሚገኘው ውስጥ 20 በመቶ ” የአንዳርጋቸው ፅጌን መስመር በመከተል ለምነወዳት ኢትዮጵያ ህይወታቸውን ለመስጠት ዱር ቤቴ ላላችሁ የነፃነት ታጋይ አርበኞች ይሁንልኝ” በማለት 120 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል።
   እንዲሁም ፤  ” ጥላሁን ያረፈ ቀን” ከሚለው መፅሀፍ ሽያጭ 50 በመቶ  ክንፈሚካኤል ደበበ( አበበ ቀስቶ) ህክምና እንዲሆን ስጦታውን አበርክቷል። በመጀመሪያው ዙር ለአበበ ቀስቶ 120 ሺህ ብር በወቅቱ እንደደረሰው ለማወቅ ተችሏል ።
አሁንም ለነጻነት ተሟጋቹ እስክንድር ነጋ ፍርድ ቤት ሲቀርብ ደጋፊዎቹና ለነጻነት የሚቆረቆሩ ወገኖች ደጋፋቸውን ለመግለጽ በ አካባቢው ብቻ ስለተገኙ በአፈሳ ያለምንም ምክን ያት ከሶስት ቀን በላይ በ እስር ላይ ቆይተው ፍርድ ቤት እያንዳንዳቸው አንድ ሺ ብር ዋስ አስይዘው ወይም ከፍለው እንዲወጡ ያዘዘውን መሰረት አድርጎ ነው ድጋፉን ያደረገው።
Filed in: Amharic