>

የህወሀት ግስጋሴ የመከላከያው  ማፈግፈግ ሸዋሮቢትን እስከማስረከብ ደርሷል...!!!" (ጋዜጠኛ ጎበዜ  ሲሳይ በየኛ  ቲቪ)

የህወሀት ግስጋሴ የመከላከያው  ማፈግፈግ ሸዋሮቢትን እስከማስረከብ ደርሷል…!!!”

ጋዜጠኛ ጎበዜ  ሲሳይ በየኛ  ቲቪ ያስተላለፈው መልዕክት ባጭሩ:

 

~ ሸዋሮቢት በህወሃት ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ገብታለች::
~ ከተማዋን ሲጠብቅ የነበረውን ህዝባዊ ሃይል አስወጥተው እኛ አለን እንከላከላለን ሲል የነበረው መከላከያ አፈግፍጓል::
~ ህዝብ በራሱ ተደራጅቶ  እራሱን መከላከል ባለበት መንገድ መስራት ይጠበቅበታል እንጅ በመንግስት ላይ ያለን እምነት እና  መተማመን መቀጠል የለበትም::
~ መከላከያ  እየተከተለው ያለው ማፈግፈግ የሚለው  አካሄድ ፍጹም ስህተት ነው:: መሳሪያ እና ልብሱን እየጣለ፡  ህዝቡን እና  ህዝባዊ ሰራዊቱን ለጠላት አጋልጦ  የሚሸሸው  ልክ  አይደለም::
~ ሸዋሮቢት እና  ደብረሲና ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች ወደ ደብረብርሃን እየሸሹ ነው::
~ የህወሃት ታጣቂዎች ሸዋሮቢትን ተቆጣጥረው ወደ ደብረሲና እየቀረቡ ነው::
~ መንግስት በሁመራ  እና  በሚሌ  በኩል ሃይሉን እና ጉልበቱን  ማሳየት ሲችል በወሎ  እና  በሸዋ  ግንባር ግን ጠንከር ያለ  እርምጃ  መውሰድ አልፈለገም::  ይህ ለምን እንደሆነ  አይታወቅም::
~ መንግስት ከ110 ሚሊየን ህዝብ በላይ ደጋፊ ከጎኑ  ይዞ የሃይል እጥረት የሚል ሰበብ ማቅረብ አይችልም::
~ እኛ እየተናገርን ያለነው ዛሬ  ላይ እንዳንናገር እየተደረግን ቢሆንም  ነገ  እውነቱ ታውቆ  ታሪክ ሊጽፈው ይችላል::
Filed in: Amharic