>
5:13 pm - Tuesday April 19, 9521

የህወሀት ግስጋሴ የመከላከያው  ማፈግፈግ ሸዋሮቢትን እስከማስረከብ ደርሷል...!!!" (ጋዜጠኛ ጎበዜ  ሲሳይ በየኛ  ቲቪ)

የህወሀት ግስጋሴ የመከላከያው  ማፈግፈግ ሸዋሮቢትን እስከማስረከብ ደርሷል…!!!”

ጋዜጠኛ ጎበዜ  ሲሳይ በየኛ  ቲቪ ያስተላለፈው መልዕክት ባጭሩ:

 

~ ሸዋሮቢት በህወሃት ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ገብታለች::
~ ከተማዋን ሲጠብቅ የነበረውን ህዝባዊ ሃይል አስወጥተው እኛ አለን እንከላከላለን ሲል የነበረው መከላከያ አፈግፍጓል::
~ ህዝብ በራሱ ተደራጅቶ  እራሱን መከላከል ባለበት መንገድ መስራት ይጠበቅበታል እንጅ በመንግስት ላይ ያለን እምነት እና  መተማመን መቀጠል የለበትም::
~ መከላከያ  እየተከተለው ያለው ማፈግፈግ የሚለው  አካሄድ ፍጹም ስህተት ነው:: መሳሪያ እና ልብሱን እየጣለ፡  ህዝቡን እና  ህዝባዊ ሰራዊቱን ለጠላት አጋልጦ  የሚሸሸው  ልክ  አይደለም::
~ ሸዋሮቢት እና  ደብረሲና ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች ወደ ደብረብርሃን እየሸሹ ነው::
~ የህወሃት ታጣቂዎች ሸዋሮቢትን ተቆጣጥረው ወደ ደብረሲና እየቀረቡ ነው::
~ መንግስት በሁመራ  እና  በሚሌ  በኩል ሃይሉን እና ጉልበቱን  ማሳየት ሲችል በወሎ  እና  በሸዋ  ግንባር ግን ጠንከር ያለ  እርምጃ  መውሰድ አልፈለገም::  ይህ ለምን እንደሆነ  አይታወቅም::
~ መንግስት ከ110 ሚሊየን ህዝብ በላይ ደጋፊ ከጎኑ  ይዞ የሃይል እጥረት የሚል ሰበብ ማቅረብ አይችልም::
~ እኛ እየተናገርን ያለነው ዛሬ  ላይ እንዳንናገር እየተደረግን ቢሆንም  ነገ  እውነቱ ታውቆ  ታሪክ ሊጽፈው ይችላል::
Filed in: Amharic