>
5:13 pm - Friday April 20, 8198

"የመስቀል ዐደባባይ ማለት ምን ማለት ነው?" (ቀሲስ ደጀኔ ሽፈራው)

የመስቀል ዐደባባይ ማለት ምን ማለት ነው?”

ቀሲስ ደጀኔ ሽፈራው

     ክብርት ወይዘሮ አዳነች አቤቤ  እስኪ አንድ እጅግ ቀላል የሆነ ጥያቄ  ልጠይቅሽ::በኛ ቤተ ክርስቲያን የሕጻናት ክፍል ተማሪዎች የሚመልሱት ነው::ለመ ሆኑ:-“የመስቀል ዐደባባይ ማለት ምን ማለት ነው?”
       የድፍረት ንግግርሽን እንደ ሰማሁት መልሱን አላገኘሽውም::እንኳን ልትመልሽው በርቀት እንኳ በአጠገቡ አላለፍሽም::መልሱ ያለው በምሥራቅ ሲሆን አንቺ እየዳከርሽ ያለሽው በምዕራብ ነው:: ምዕራብ ደግሞ ይዞ የሚመጣው ጨለማን ነው:: ምሥራቅ ግን ብርሃንን ነው::አንድም ምሥራቅ ብሂል ማኅደረ እግዚአብሔር የሚለውን ጠቅሰን: ምዕራብ ብሂል … የሚለውን ግን ለጊዜው እንተ ወው::ብርሃን ዕውቀት የሚለውንም ይዘን የጨለ ማን ለጊዜው በሠላሳ እንግደፈው::
       እስኪ ወደ መልሱ እንሂድ::የመስቀል ዐደባባይ ማለት:-ክርስቶስ በደሙ ፈሳሽነት ለቀደሰው እና ላከበረው ክቡር መስቀል በአደባባይ በገሃድ የሚሰገድ በት:የመስቀል ክብር በንባብም በዜማም የሚገ ለጥ በት ስፍራ ነው::መዝ:131%7::”የመስቀሉ ቃል ለሚ ጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብ ሔር ኃይል ነው::”ተብሎ የሚታወጅበት:”ከጌታችን ከኢየ ሱስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ክእኔ ይራቅ:: “የሚባልበት  መቅደስ ነው::1ኛ::ቆሮ:1%18::ገላ:6% 14::ይህንን ደግሞ ከጥንት ጀምሮ በራሷ ይዞታ ላይ ስትፈጽም የኖረችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ናት::የመስቀል አደባባይ ብላ የሰየመ ችውም እርሷ ናት::አንቺም በባለቤትነት ሳይሆን በእንግድነት በበዓለ መስቀል ላይ እየተገኘሽ ንግግር አድርገሻል:ደመራ ለኩሰሻል::ቤተ ክርስቲያን ባታከብ ሯትም እርሷ ግን እንዲህ አድርጋ ነው የምታከብራ ችሁ::
        ታድያ የመስቀል አደባባይ ትርጉም ይሄ ከሆነ ክብረ መስቀልን በአደባባይ ከካዱ አክራሪ ፕሮቴስታ ንት  እና  ነገረ መስቀሉ ከማይመለከታቸው አክራሪ ሙስሊሞች ጋር ምን አገናኘው? ምንም::ሰሞኑን ሕወሓት ከጦርነቱ ባሻገር መንግሥትን እና ሕዝብን እየዘረፈ ነው እያላችሁ ነው::እውነት ነው::አንቺስ በሥልጣንሽ ተመክተሽ:ለእምነት ድርጅትሽ አድል ተሽ ከጥንት ጀምሮ ይዘን የኖርነውን ይዞታችንን በጠራራ ፀሐይ ትዘርፊናለሽ? ለመሆኑ ለጎሳሽም ለእሬቻም ለፕሮቴስታንትም እያደላሽ እንዴት ነው ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ስትዪየከረምሽው? ያ የትኅትና ንግግርስ ከምን ግዜው ጠፍቶ ነው ወደ ትዕቢት  ንግግር  የተመለስሽው? መስቀል አደባባይ እኮ የ65 ሚሊዮን ኦርቶዶክሳውያን ርስት ነው::ኢትዮጵያም ከጥንት እስከ ዛሬ ሰማዕትነት የከፈልንላት ታቦት እና መስቀል ይዘን ዳዊት አንግተን የዘመትንላት ርስታ ችን ናት::በመሆኑም ኢትዮጵያ እንደ ሀገር የጋራችን: የአምልኮ ስፍራችን ግን የግላችን ነው::
      ወደ መፍትሔው እንሂድ::መፍትሔው ምን መሰለሽ? ሌሎች ሁለት አደባባዮችን ሥሪ እና አንደ ኛውን ኢድ አደባባይ በዪው ሁለተኛውን ደግሞ ፓስተር አደባባይ በዪው::በተረፈ ስለ መስቀል አደ ባባይ የተናገርሽውን በባለቤቱ ፊት እንድትናገሪው
ለመስከረም 16 ቀን 2015 ብታቆዪው መልካም ነው::
ሀገር በውስጥም በውጭም በተወጠረችበት በዚህ የጭንቅ ወቅት ለሕዝቡ የሚከፋፍል አጀንዳ ባትፈ ጥሩለት  ጥሩ ነበር::
አባቶች በመግለጫ የሚመለስ መከራ የለም…!!!
   ቤተክርስቲያን ስትቃጠል መግለጫ::ካህናትና ምእመናን ሲታረዱ መግለጫ::የዐደባባይ በዓላትን እንዳታከብር እንቅፋት ሲፈጠር መግለጫ::በዐውደ ምሕረቷ የሰቀለቻቸው:ምእመናን የለበሷቸውና ከበሮዎቿን ጭምር ያለበሰቻቸው ሰንደቅ ዓላማዎች እየውረዱና እየተገፈፉ ሲጣሉ መግለጫ::የጥምቀተ ባሕርና የመስቀል አደባባይ ቦታዎቿ ሲነጠቁ መግ ለጫ::ለሁሉ ነገር መግለጫ:መግለጫ:መግለጫ::
ሰሚ ግን የለም::እንኳን የሚሰማ የመስማት ፍላጎት እንኳ ያለው የለም::አትድከሙ::
        እባካችሁ አባቶች ለሀገራችሁ  እና ለቤተ ክርስቲያናችሁ የምታስቡ ከሆነ እነርሱ መግለጫ ከማውጣት በስተቀር ምንም አያመጡም እየተባላችሁ መንጋውን አታስበሉ::ፈረጅያችሁን አውልቃችሁ በአጭር ታጥቃችሁ ከልጆቻችሁ ጋር ተሰለፉ:: ደረጃ ውን ከጠበቀ ቢሮ ተቀምጣችሁ የምታወጡት መግለጫ ከሚድያ ፍጆታነት አያልፍም::
       ከልቤ የምወዳችሁ እና የማከብራችሁ አባቶቼ በመግለጫ ጋጋታ የሚመለስ መከራ የለም በጸሎት እና በትግል ነው::
Filed in: Amharic