>

በኦሮሚያ ክልል በማንነት ላይ ያነጣጠረ ተደጋጋሚ ግድያ...!!!  D W

በኦሮሚያ ክልል በማንነት ላይ ያነጣጠረ ተደጋጋሚ ግድያ…!!!

 D W

ኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ውስጥ 168 ሰዎች በማንነታቸው ተለይተው መገደላቸው ሰሞኑን ብርቱ ቁጣ ቀስቅሷል። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሰኞ ዕለት የቄለም ወለጋ ዞን አስተዳደር ተወካይና የዞኑ አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብሣ በሻን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፦ በኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት «ሸኔ» በሚል ስም በሽብርተኝነት የተፈረጀው ራሱን «የኦሮሞ ነጻነት ጦር» ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን ሰላማዊ ሰዎችን በአካባቢው በጅምላ ገድሏል።
በክልሉ የዐማራ ተወላጆች በተደጋጋሚ በታጣቂዎች አሰቃቂ ግድያ ሲፈጸምባቸው ይስተዋላል።
የቄለም ወለጋ ዞን ፀጥታ አስተዳደር ኃላፊ አቶ ተሰማ ዋሪዮ ለወራት በታጣቂዎች ስር የነበረው ጊዳሚ ወረዳን ሰሞኑን ወደ መንግስት አስተዳደር መመለሱን ገልጠው ግድያው ገና አለመጣራቱን ትናንት ለዶይቸ ቬለ (DW) ተናግረዋል።
ለመሆኑ በተለይ ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ማንነት ላይ ባነጣጠረ ጥቃት በተደጋጋሚ ጥቃት የሚደርስባቸውን የዐማራ ተወላጆች የክልሉም ሆነ የፌዴራል መንግሥት በምን መልኩ ጥበቃ ሊያደርግላቸው ይገባል?
በኦሮሚያ ክልልም ሆነ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች በተለያየ ጊዜ ማንነትን መሠረት ያደረጉ ግድያዎችን ለማስቆምስ ምን መደረግ አለበት ትላላችሁ?
Filed in: Amharic