>
5:14 pm - Tuesday April 20, 9486

ለማን አቤት ይበል?! (ጌታቸው አበራ)


ለማን አቤት ይበል?!

   (በአገራቸው ምድር ላይ ፍትህና ርትዕ ተነፍገው ለሚሰቃዩ 

 የአገሬ ሰዎች በሙሉ)


በዚያ መልካም ዘመን – ግብረገብ ሳይተን፣

ጎበዝ ያገሬ ሰው – በእምነት የታነጸው፣

ሙስሊም፣ ክርስቲያኑ.. – የዋሁ ምስኪኑ፣

ጥቃት ሲደርስበት – ፍትህ ሲጎድልበት፣

በህግ አምላክ ካለ – በሰንደቅ ከማለ፣

አጥፊም ይታቀባል፤ – ጠላትም ይቆማል፤

     ••••••••••••

ዛሬ ክፉ ጊዜ  – የዘመን አባዜ፣

ሰንደቁ ተረግጦ – ፍትህ ‘ድሜ’ ግጦ፣

ማተብ ተበጥሶ – እምነት ተቀንጥሶ፣

ርህራሄ ተኖ  –  እርኩሰቱ ገኖ፣

 ጠባቂ ነኝ ባዩ  – መንግስት አስገዳዩ..፣

ሆኖ ሲገኝ ከቶ – በአገር መላ ጠፍቶ፣

በተፈጠረባት በዚህች በምድሪቱ፣

 ለማን አቤት ይበል? ዜጋ ለህይወቱ!

 

ጌታቸው አበራ

የካቲት 2014 ዓ/ም

(ፌብሯሪ 2022)

Filed in: Amharic