>
5:13 pm - Sunday April 19, 0144

የፖለቲካ ድኩማኖች አለም አቀፍ ጦርነት በመቀስቀሱ ጮቤ እየረገጡ ነዉ...!!! (ሸንቁጥ አየለ)

የፖለቲካ ድኩማኖች አለም አቀፍ ጦርነት በመቀስቀሱ ጮቤ እየረገጡ ነዉ…!!!
ሸንቁጥ አየለ

የአቢይ አሽቃባጭ የፖለቲካ ተንታኞች የሩሲያን ወረራ ጉዳይ የአማራ ህዝብ እልቂት ለማዳፈኛነት ሊጠቀሙበት እየተጯጯሁ ነዉ::እንሱ በጮሁ ቁጥር አብሮ የሚጮህ ብዙ ቁራዎችም አግኝተዋል::
መከራ እና ሰቆቃ ዉስጥ ስለ ወደቀዉ አማራ ትንፍሽ ሳይሉ የሰነበቱት ምናምንቴዎች አሁን ደርሶ የሰበአዊ መብት እና የወታደራዊ ሳይንስ ጠበብት በመሆን የተወለጋገደ ትንታኔ እያዘነቡ ነዉ::
ያዉ የተሰጠዉን አጀንዳ እየለቃቀመ ሲጮህ የሚዉለዉ ብዙሃንም የራሱ ዜጎች/ የራሱ ነገድ የዘር ፍጅት ታዉጆበት አይኑ ስር በአሬመኔዎች ሰይፍና ርሃብ እያለቀ ይሄን ጉዳይ ጥቅጥቅ አድርጎ በመዝጋት የሩቅ ጉዳይ ከንፈር መጣጭ ሆኗል::
—-
ለማንኛዉም ፖለቲካ ካወቃችሁ ነገሩ የግራ የሆነዉ ለምትጨፍሩለት  ለአለቃችሁ ለአቢይ ነዉ::
አለቃችሁ አቢይ ወይ ከምዕራብ መወገን ወይም ከሩሲያ መወገን ይኖርበታል::ምዕራባዉያን እግር ስር ወድቆ እየተማጸነ ወልቃይትን እና ራያን ለወያኔ መልሼ ከወያኔ ልታረቅ ብሎ ሲማልድ የሚዉለዉ የአቢይ መንግስት ከምዕራባዉያን በኩል ከእኛ ጋር ነህ ወይስ ከሩሲያና ቻይና ጋር ነህ የሚል ጥያቄ ይቀርብለታል::ጥያቄዉን በአፍ አክሮባት መመለስ አይቻልም::ጠላቶቻችን ሰድበህ እና ረግመህ ከአተገባቸዉ ርቀህ በተግባር አሳዬን ይባላል::
የሩሲያ ወዳጅ ነኝ ብሎ በምላሱ የሚዘላብደዉ የአቢይ መንግስት ከሩሲያም የማረጋገጫ የወዳጅነት ጥያቄ በቅርቡ በግልጽ ይቀርብለታል::ከጥያቄዎቹ አንዱ የተባበሩት መንግስታት በሚያደርገዉ ጸረ ሩሲያ ዉሳኔ የአቢይ መንግስት ዉሳኔዉን ተቃዉሞ ከሩሲያ ጋር እንዲቆም ቃላችሁን ስጡን የሚል ጥያቄ ይቀርብለታል::
አቢይ ደግሞ ሁለቱንም ማድረግ ስለሚፈራ የኩበት ላይ ዉሃ ሆኖ ተንሳፎ ይቀራል እንጂ ሩሲያንም ሆነ አሜሪካንን ወግኖ አይሰለፍም::በአንድ ሌሊት ጨረቃ ሰባት ጊዜ ምልሎ ሰባት ጊዜ በመካድ ስልጣን መጨበጥን እንደ ትልቅ ክህሎት የሚመለከተዉ የኦህዴድ/ኦነግ ሀይል የአማራን ዘር ከምድረ ገጽ ለማጥፋት አለምን በማጨበርበር እንደተሳካለት ሁሉ ሩሲያን/አሜሪካን ለመሸወድ መሞከሩ ግን አይቀርም::
ሆኖም የምዕራባዉያንም ሆነ የሩሲያ ከኛ ጋር ቁም ጥያቄ የአማራን ህዝብ የሚጨፈጭፈዉ/የሚያፈናቅለዉ ኦነግ ሸኔ ነዉ ብሎ ለማታለል እንደመሞከር ቀላል አይሆንም::
የአቢይ መንግስት በሩሲያ/ቻይና እንዲሁም በምዕራባዉያን መሃከል በተፈጠረዉ ፍጥጫ ከሚጎዱት የመጀመሪያ ሀይሎች ዋና እና ቀዳሚዉ ብቻ ሳይሆን ህልዉናዉ የሚያከትምበት ሁሉ ሊሆን ይችላል::
ያገጠጠዉ የአለም አቀፍ ጦርነት እና ግጭት ዉጤት ይሄ ነዉና የአቢይ ጭፍራዎች ብዙም አትደንሱ::ብዙም አትጯጯሁ::
Filed in: Amharic