አልጋና ጾም…!!!
ያሬድ ሀይለማርያም

ይህ ታሪክ ነገስታቱ በዛ ዘመን ለሀይማኖታቸው ያላቸውን ቀናይነት ብቻ ሳይሆን የሚያሳየው ለሚስቶቻቸው ያላቸውንም ክብርም ያሳያል። ጾም ሲፈታም ‘ካልጋ ወድቄ ነበር’ ብሎ ከመናዘዝና ከሀጢያቴ ይፍቱኝ ከማለትም ያድናል። የተደራራቢ አልጋ ሥራ ጽንሰ ሀሳብም መነሻው ከወዴት እንደሆነ ያመላክታል። ከዚህ አልጋ አጠገብ ደግሞ በ1307 ዓ.ም የተሠራውና ከ700 አመታት በላይ እድሜ ያስቆጠረው የንጉስ አምደ ጽዮን አልጋ ከነመጎናጸፊያው ይገኛል።
እንግዲህ የሁዳዴን ጾም የምትጾሙ ባለትዳሮች ይችን የንጉስ ተክለሀይማኖትን ተደራራቢ የጾም ወቅት አልጋ ቢያንስ ቢያንስ ብትጎበኟት ጥሩ ነው።