>

አዲስ አበቤ ከዩኒቨርስቲዎች እስከ መንደሮች የአፈሳና  የሽብር ዘመቻ ተከፍቶበታል...!!! (ዘመድኩን በቀለ)

አዲስ አበቤ ከዩኒቨርስቲዎች እስከ መንደሮች የአፈሳና  የሽብር ዘመቻ ተከፍቶበታል…!!!
ዘመድኩን በቀለ

“… በጅምላ እየታፈሱ ያሉትን ወጣቶች ፍርድቤቶች የዋስትና መብት እንዳይሰጧቸው መመሪያ ተላልፎላቸዋል! ዋስትና የለም…!!!
ከውስጥ አዋቂ የተገኘ መረጃ …!!!
 
“…በአዲስ አበባ በመንግሥት ትንኮሳ ምክንያት ከዓድዋ ድል በዓል ማግሥት ጀምሮ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአዲስ አበባ ወጣት እየታሰረ ነው። ይህንን እስር (አፈሳ) በበላይነት እየመሩ ያሉ አካላት ደግሞ አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ ጀነራል ኮሚሽነር ደምመላሽ ገብረ ሚካኤል፣ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ ፋንታ፣ ከንቲባ አዳነች አበቤ እና ምክትል ኮሚሽነር ሀሰን መሀመድ ናቸው። ዋነኛ ዓላማቸውም የአዲስ አበባን ወጣትም፣  ህዝቡም እንዲማረር እና ብን ብለው እንዲጠፉ፣  እንዲሰደዱ፣ በሞትም እንዲቀነስ ማድርግ ሲሆን የተቀረው ደግሞ የበታችነቱን በፀጋ አምኖ እንዲቀበልና አንገቱን ደፍቶ እንዲኖር ለማድረግ ነው።
“…በቀጣይ ወራት ውስጥ አዲስ አበባ ከሌሎች ብሔር ብሔረሰቦች የጸዳች፣ ልክ እንደ አንድ የኦሮሚያ ከተማ የሆነች ከነ ስሟም አዲስ አበባ ፊንፊኔ ተብላ የምትጠራ ከተማ ለማድረግ እየተሠራ ሲሆን ለዚህም በጀት ተመድቦ እስከ15,000 (አስራ አምስት ሺህ) ወጣት በማፈስ ኦሮሚያ ክልል ወደሚገኙ ወታደራዊ ማስልጠኛ ተቋማት በመውሰድ ከዚህ ቀደም ህወሓት ስታደረገው እንደነበረው ከሞት የተረፉትን ወጣቶች “አይደገምም” የሚል ቲሸርት አስለብሳ ስታሰቃይ እንደነበረው ለማድረግ አፈሳና እስራቱን በሰፊው በማጧጧፍ ላይ ይገኛል።
“…አሁን ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ እስር ቤቶች በሙሉ በአዲስ አበባ ወጣቶች ተሞልተዋል። የፌደራል ማቆያ ቦታዎችም ሞልተዋል። ከከተማ ደር የሚገኘው የአባ ሳሙኤል ማረሚያ ቤትም ሞልቷል። እያንዳንዱ የፌደራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የሲቢል ክትትል ፖሊሶች፣ እንዲሁም የብሔራዊ መረጃ ደህንነት፣ የሀገር መከላከያ (የኢንተለጀንስ) ባለሞያዎች፣ በኮታ መልክ እያንዳንዳቸው አባላት ከዓድዋ በአል ጀምሮ የካራማራን በአል ያከበሩ፣ እንዲከበር ያስተባበሩ፣ በበአላቱም ላይ የተገኙትን፣ ከ30-40 በብሔር ሳይመርጡ በተለይ ግን የዐማራ፣ የጉራጌና የጋሞ፣ የደቡብ ልጆችን እንዲያፍሱ ታዘዋል። በዚህም መሠረት እየያዙም ነው። የተያዙትን ወጣቶች ፍርድቤቶችም የዋስትና መብት እንዳይሰጡም መመሪያ ተላልፎላቸዋል። ዋስትና የለም።
“…አሁን በኑሮ ጫና የተማረረው የከተማ ነዋሪ በሰፊው ለአመጽ እንዲነሣና አመጹን ተከትሎ በዕቅዳቸው መሰረት አፈሳውን ለማጧጧፍ ከዓደዋ በዓል ምሽት ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግጭት እንዲፈጠር እያደረገ የሚገኘውም ራሱ መንግሥት ነው። ያውም ለዐመፁ ቀስቃሽ ቄሮዎቹ በጀት መድቦ፣ ወጣቶችን ቀጥሮ ብጥብጥ እንዲነሳ እያደረገ ያለውም ራሱ መንግሥት ነው። የዐመጹም መሪ ኢብሳ ይባላል። ከዚህ ቀደም የታከለ ኡማ ተላላኪ እና በየቦታው ግጭት ፈጣሪ የነበረው ኢብሳ የሚባለው የኦሮሞ ባለ ጎፈሬ ወጣት አሁንም ከንቲባ አዳነች አቢቤና ኦቦ ሽመልስ አብዲሳ አነጋግረው ቀጥረውት ወደ ብጥበጣ ሥራው በነፃነት እንዲገባ ተደርጓል።
• ማስታወሻ፦ የዐማራ ተወላጅ ሆነው ከፍተኛ ውጤት ያላቸው ሰቃይ ተማሪዎች በዚህ ብጥብጥ ሰበብ ከተቻለ እንዲገደሉ ካልተቻለ ደግሞ አካለ ስንኩል እንዲሆኑ እንዲደረግም መመሪያ ለአማፅያኑ ቄሮዎችና ጸጥታ ለማስከበር ወደ ዩኒቨርሲቲው ለሚሰማሩት የኦሮሚያ ፖሊሶችም መመሪያ ተሰጥቷቸዋል። እናም የሌላ ብሔር ተወላጅ ተማሪዎቹ ለጊዜው ጥንቃቄ ያደርጉ ዘንድም ቢነገራቸው መልካም ነው ተብሏል። እንዲያው ለነገሩ ነው እንጂ ሚሽኑ የወንዶችም ሆነ የሴቶችን ዶርሞች ሰብረው ሁላ በመግባት ጥቃት እያደረሱ ነው። በነፃነት ሰልፍ እያደረጉ ነው። ሌላውን ብሔር እየሰደቡ፣ እያንቋሸሹም ነው። በስድቡ የሚጣላቸው ሲያጡም በዊልቸር የሚሄድ አንድ ተማሪ ደብድበው በሞትና በህይወት መሃል ጥለውት አሁን በህክምና ላይ ነው። ትናንት ሌሊትም ብዙ ተማሪ ተጎድቷል።
“…ይህን ሁሉ የሚያደርገው ቄሮ ኢብሳ አብሪሻ እና ጓደኞቹ ቄሮ ጫላ ከድር እና ቄሮ ኤርምያስ አበራ የተባሉ ሲሆኑ፣ ቄሮ ኢብሳ አብራሻ ሁልጊዜ የማይመረቅ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ3ተኛ ዓመት ተማሪ ሆኖ በዩኒቨርሲቲው የሚኖር ሲሆን ከዚህ በፊትም ኦብሳ አብዲሳ በመባል ይጠራ የነበርና በታከለ ኡማ ጊዜ በባልደራስ ጽሕፈት ቤት በመገኘት አቶ እስክንድር ነጋ ላይ ጥቃት ለመፈጸም ሲጋበዝ የነበረ ጽንፈኛ የኦሮሞ ወጣት የነበረው ሰው ነው። ይህሰው በሲዳማ፣ በሀረርጌም በመዞር ብዙ የክርስቲያን ኦርቶዶክሳውያን እና ዐማሮችን ደም እንዲፈስ ያደረገ አረመኔ ኢትዮጵያ ጠል የሆነ ሰውም ነው ይላሉ የመረጃ ምንጩ። ቄሮ ኢብሳ/ኦብሳ አሁን የራሱን ደግሞ ቄሮ ፊንፊኔ የሚል ስያሜ የተሰጠው ቄሮዎችን በማደራጀት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ እና ከዩኒቨርስቲው ውጭ ግጭት እንዲፈጠር እየሠራ የሚገኝ ሲሆን ፖሊስም ልጁን እንዳያስረው፣ አካላዊ ጥቃትም እንዳያደርስበት ተነግሮታል። በኢብሳና በቡዱኑ ዙሪያ ለፌደራል አመራሮችም፣ ለአዲስ አበባ ፖሊስ አመራሮች እና ለአስራ አንዱም ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አዛዞች በምክትል ኮሚሽነር መላኩ ፋንታ ቢሮ ድረስ ተጠርተው ጫፉ እንዳይነካም  እንደተነገራቸው ተሰምቷል። በተሰጠው መረጃ ላይ ተቃውሞ አለን የምትሉ በሩ ክፍት መሆኑን ለመግለጽ እወዳለሁ።
“…የአዲስ አበባ መከራዋ ገና እየጀመረ ነው። ከዚሁ ጎን ለጎን በአቶ ተመስገን ጥሩነህ እና ኤርትራ በረሃ ሲሰለጥኑ በነበሩ በግንቦት 7 እና በኦነግ ገዳይ ስኳድ ቡድኖች የተዋቀረ አንድ ነፍሰበላ የሆነ ቡድን በዐማራ ክልል የሚገኙ ፋኖዎችን፣ ባለሃብቶችን፣ በሃይማኖታቸው የሚከበሩ ዜጎችን አንድ በአንድ ቀስበቀስ ሁሉንም ገድሎ እንዲጨርስ መመሪያና ትዕዛዝ ወርዶለት ግዳጅም ተሰጥቶት ወደ ተግባር በመግባት የጎጃም፣ የጎንደር፣ የወሎና የሸዋ ፋኖዎችን እየመነጠረ፣ በየበራፋቸው፣ በየደጃፋቸው እየደፋ ይገኛል። አቶ ተመስገን ጥሩነህ ከዶር ዐቢይ እና ከመከላከያ ሚንስትሩ ዶር አብርሃም በላይ ጋር የሚመሩትና ወደ ዐማራ ክልል የላኳቸው ገዳይ ስኳድ የመከላከያ፣ የፌደራል ፖሊስና የዐማራ ክልል የደንብ ልብሶችን ለብሶ እንዲንቀሳቀሱም መመሪያ ማወረዱም ነው የተሰማው። ብልፅግናም ይመጣብኛል ብሎ የሚያስበውን ህዝባዊ ማዕበል በዚህ መልኩ የጭካኔ ተግባር ሌሎችን በማሸማቀቅ ለማለፍም እየደከመ ነው። እርግጥ ነው መጪው ጊዜ ከባድ ነው። ክብደቱ ግን ለብልጽግና ይብስበታል።
• መልካም የአፈሳ እና የጅምላ እስር ዘመን ይሁንልን።
• መልካም በተመስገን ጥሩነህ የገዳይ ቡድን የመሞቻ፣ በየደጃፍህ የመደፊያ ዘመን ይሁንልን።
• እንዲህም ሆኖ ብልፅግና በቅርቡ ከነ ስም አጠራሩ መውደሙ አይቀርም።
“… ሻሎም !   ሰላም !
Filed in: Amharic