ዕረፍቱ ለቴዎድሮስ ንጉሠ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ…!!! (ታደለ ሲሳይ)

ዕረፍቱ ለቴዎድሮስ ንጉሠ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ…!!!

ታደለ ሲሳይ

ትላንት ሊበታትኗት የቋመጡላት ኢትዮጵያ ከዐፄ ቴዎድሮስ በፊት ተበታትና ነበር። በመሣፍንት የሥልጣን ጥማት እንደ ቅርጫ ሥጋ የተበታተነችው ኢትዮጵያ ማእከላዊ መንግሥት አልነበራትም። ነገር ግን የቋራው ካሣ ተነሥቶ የሥልጣን ጥመኞችን ወሽመጥ ቆርጦ የተበታተነውን የኢትዮጵያ ሥጋ ሰብስቦ የአንድነት መለከት ነፋበት። ግኡዙ ሥጋም እስትንፋስ ነሥቶ ኢትዮጵያ በአንድ መንግሥት መመራት ጀመረች።ዘመነ መሣፍንትም ታሪክ ሆነ። እነሆ ይህ ንጉሥ ትላንት የዕረፍቱ መታሰቢያ ነበረ።
በቴዎድሮስ የጠፉት መሳፍንት ዛሬ በየቦታው ብቅ ብቅ ብለው የየራሳቸውን ግዛት አጥረዋል። ጦራቸውንም አሠልጥነዋል። ኢትዮጵያ ከማእከላዊ መንግሥትነት ወደ መሣፍንት ዘመን ተመልሳለች። ይህንን የሥልጣን ጥመኛ ሁሉ አንበርክኮ አንድነቷን የሚመልስ ግዛቷን የሚያጸና ጀግና ያስፈልጋታል። በቴዎድሮስ አማካኝነት የተበታተነችውን ኢትዮጵያን አንድ ያደረገ አምላክ በጎጠኞች የተከፋፈለችን ኢትዮጵያ አንድ ለማድረግ ጀግና እንደሚያስነሣ እምነታችን ጽኑ ነው።

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.