>

ጽንፈኞች ሶስተኛውን ቤተክርስቲያን አቃጥለዋል...!!! (ዘመድኩን በቀለ)

ጽንፈኞች ሶስተኛውን ቤተክርስቲያን አቃጥለዋል…!!!
ዘመድኩን በቀለ

 

… አሁናዊ አጫጭር መረጃዎች… 
 
* …. “በፋሲካ ማግስት ፆም ስግደቱ ሲቆም ፀሎቱ ተረሳ
እኛ መሞት ጀመርን አንተ ስትነሳ”
 
•… ጎንደርን ሲተራመሱ፣ ህዝብንም ሲረሸኑ፣ በከባድ መሳሪያም መከላከያን ጭምር በየፎቁ ላይ ሆነው ሲገጠሙ የዋሉት አሸባሪዎች ገሚሶቹ በቁጥጥር ስር ውለዋል። አንደኛው አሸባሪ ደግሞ ከሌላ ክልል የሄደ አሸባሪ መሆኑ እየተነገረ ነው። ሌሎቹ ወጪት ሰባሪዎች ደግሞ እዚያው ጎንደር ተወልደው ያደጉ መሆናቸው ተነግሯል።
• በዐቢይ አህመድ እውቅና፣ በአህመዲን ጀበል መመሪያ ሰጪነት፣ በሙጂብ አሚኖ ሥምሪት ሰጪነት በስልጤ ወራቤ እስከ አሁን ሁለት አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል። አንዱማ ቤንዚን ተርከፍክፎበት ነው የወደመው።
“…በስልጤ ወራቤ የሚኖሩ ክርስቲያኖች በሙሉ ሀብት ንብረታቸው ወድሟል። ተደብድበዋል። ተገድለዋል። ጴንጤዎች ናቸው አትንኳቸው የሚሉ የነበሩ ቢኖሩም ያው ካፊር ናቸው በሚል 3 የጴንጤዎች ቸርች መቃጠሉም ተሰምቷል። የስልጤው የዛሬ ውሎ በፅንፈኞች ሲወደስ ውሏል።
• ጠቅላይ ሚንስትሩም ሆነ እስላማዊ መንግሥታቸው ዝምታን መርጧል። የቱርኩ የኤርዶጋን መንግሥት መግለጫ አውጥቷል። ቱርክ ለዳግማዊ ግራኝ አሕመድ ጥብቅና ለመቆም የፈለገች ይመስላል። በትግራይ ክልል ኦርቶዶክሳውያንን ሲያርድ የከረመው የዳግማዊ ግራኝ ዐቢይ አህመድ መንግሥት በአረቦቹ ዘንድ ልዩ ክብር እያገኘ መምጣቱን አስመስክሯል።
“…የስልጤ ፖሊስ ራሱ አላህ ወአክበር እያለ ክርስቲያን በተለይ ዐማራ የሆኑትን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሲደበድብ ውሏል። የገደሉትም አለ። ጉዳት የደረሰባቸው በሙሉ በስልጤ ወራቤ ህክምና መከልከላቸውን ነው እየነገሩኝ ያሉት። ከመላ ሃገሪቱ ስልጤ ወራቤ ዩንቨርስቲ የሄዱ ተማሪዎች መሄጃ አጥተው፣ የሚጠብቃቸው ፖሊስ አጥተው በጭንቀት እያወሩኝ ነው። ቪድዮዎቹን በቴሌግራም ቻናሌ ላይ ይመልከቱ።
• ኡስታዝ አህመዲን ጀበል
• ኡስታዝ ከሚል ሸምሱ
• ኡስታዝ በድሩ ሁሴን
• ኡስታዝ አቡበከር አህመድ
• ኡስታዝ ያሲን ኑሩ
• ሙጂብ አሚኖ ፦ ስሙኝ ልንገራችሁ። አሁን በስልጤ እየሞቱ፣ እየተደበደቡ፣ እየተደፈሩ ያሉት ህፃናት ክርስቲያን ተማሪዎች እናንተ ተንፈላሳችሁ በምትኖሩበት አዲስ አበባ ከተማ እንዴት ያሉ ወንድሞች፣ አባት፣ ዘመድ አላቸው መሰላችሁ። በእውነት እውነቴን ነው። ተዉ ይቅርባችሁ። ወላጆች ለእነዚህ ኡስታዞች በመደወል የልጆቻችሁን ጉዳይ አሳስቧቸው። የኡስታዞቹ ስልክ ያላችሁ ካላችሁ ብታቀብሉኝ እኔም ለሁላችሁ እለጥፍላችኋለሁ። ወዲህበሉኝ።
“…የሚገርመው ነገር የአህመዲን ጀበል ቡድንም ሆነ ስልጤው ሙጂብ አሚኖ ለሕግ የማይገዙ ከባዶች ሆነው አይደለም። እነርሱ እንዲህ እንዳሻቸው የሚፏልሉት የተማመኑትን ተማምነው ነው። ዘመን ግን ይመጣል። እንዲህ እንደ ሆነም አይቀርም። የሰውም የአምላክም፣ የምድርም የሰማይም ፍርድ ቅርብ ነው።
ጂሀዲስቶቹ ቂልጦ ቅድስት ማርያም ገዳምን አቃጥለዋል ‼
በዛሬው ዕለት ከምሽቱ 6 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ላይ የእስልምና አክራሪ ኃይሎች በስልጤ ዞን 3ተኛውን ቤተ ክርስቲያን በምሥራቅ አዘርነት በርበሬ ወረዳ የምትገኘውን ቂልጦ ቅድስት ማርያም ገዳምን አቃጥለዋል ‼
የሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ የሚሰማን አጣን ወደማን እንጩህ ከቀን ጀምሮ የጥፋት ዝግጅቱ ከፍተኛ ነው እያልን ስጋት ያለባቸውን አብያተ ክርስቲያናት ለቅድመ ጥንቃቄ ብለን በመዘርዘር ከመግለጫ ጭምር አሳሰብን በስልክ የምንነግራቸው የልዩ ኃይል መሪ ስልካቸውን ዘግተው ጠፉ  ለጽንፈኞች የእሳት እራት አደረጓት ሲሉ በፌስቡክ ገጻቸው አስታውቀዋል።
በግቢው የነበሩ ካህናት ጥቂቶቹን የአካባቢው ፖሊስ አትርፎ ፖሊስ ጣቢያ ደብቋቸዋል። ሌሎች የት እንዳሉ አልታወቀም ሲሉ ነው ያስታወቁት ዋና ሥራ አስኪያጁ።
ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል – Wiirtuu Miidiyaa Tewaahidoo – TMC
“… እየታዘባችሁ…!!
በጦቢያ_የግጥም_ምሽት ላይ’ ኢትዮጵያ አትፈርስም የሚለው የዕለቱ ተጋባዥ እንግዳ ንግግር ሲሰማ’ ታዳሚው በጭብጨባ አዳራሹን ያቀልጠዋል!!
#ደግሞ’ እንደፋሽንም ሆነ’ እንደ አዳማቂ ነገር ተቆጥሮ ይሁን ከሙስሊሙም፥ ከክርስቲያኑም ጎላ ጎላ ያሉት ተመርጠው ነው ኢትዮጵያ አትፈርስም የሚሉን።ግን #ሪሊ’ ኢትዮጵያ አትፈርስም?
#ዐብይ_አህመድ’ በማስተኛው የእንቅልፍ ኪኒኑ ኢትዮጵያ አትፈርስም ሲልህ የእጅህ መዳፍ አይደለም በጭብጨባ የሚላጠው፣ የተቀመጥክበት ወንበር መቀመጫህን እስኪቦርሸው ድርስ ስትጋጋጥ ያጨበጨብክ ሁሉ ኢትዮጵያ’ ያለመፍረስዋን እያየህ ነው።
#አገር_አለኝ ብለህ ህንጻ ስትገነባ’ ያማረ ቪላህን ስታንጽ’ #ዳሩ_አገር መሀል መሆኑን ዘንግተህ ከአዲሶቹ ገዥዎች ጋር’ ስትሞዳሞድ #አዲስ_አበባ_እንደስልጤ_ዞን የሚል መጽሃፍ ታትሞ እንደምታነብ አትጠራጠር። ለዚያውም አገር ሙሉ ለሙሉ ካልወደመች ነው የምታነበው።
#መሪው’ በተምኔታዊ ዐለም ውስጥ መርቅኖ’ ኃይማኖታዊ በዓላት በመጡ ቁጥር ከሙስሊሙም፥ ከክርስትናውም ዙርያ ያሉ ፈሪሳውያን አማካሪዎቹን ቃል ኮርጆ ወስዶ በመደረት በቅዱስ መጸሃፍ ቃል አጅቦ’ ያስተኛሀል። ቃልና ተግባር ግን በአገሪቱ በፍጹም የሉም።
የመኖር ዋስትናህ ምንድነው? #ወራቤ ከአዲስ አበባ ስንት ኪሎሜትር ነው? የሚነደው ጭስ አይታይህም? የጭሱ ቋያ በቅርብ #በበራሪ ከወራቤ አዲስ አበባ እንደሚደርስ አትጠራጠር፣ ምክንያቱም በሀገሪቱ ተቋም የለማ! ተቋም አብይ አህመድ ብቻ ከሆነ አራት አመት ሞላው። ሰውየው የመደመር መጽሃፌ ብቻ ነው #ተቋም ብሎ’ አገር እየፈራረሰችና እየነደደች እሱ ሌክቸር ይሰጣል! ቆስጣ ያስጎበኛል! በተምኔታዊ’ ዓለም #አራምባውን እየሳበ ይቃዣል! የዚህ ዓይነት መሪ ነው ያለህ! እረፈው!
Filed in: Amharic