>

የአገሪቷ ቀውስ ስር እየሰደደ ነው፤ የብልፅግና መንግስት አልቻለም....!?! (ግርማ ካሳ)

የአገሪቷ ቀውስ ስር እየሰደደ ነው፤ የብልፅግና መንግስት አልቻለም….!?!

ግርማ ካሳ


*… ካለንበት ቀውስ መውጫ ቀዳዳ ካልተፈለገ አሁን ባለንበት ሁኔታ መቀጠል አንችልም፤ በመሆኑም  ገዢው የብልፅግና  ፓርቲን ያካተተ የሽግግር መንግስት  ያስፈልጋል…!!!

የሽግግር መንግስቱ ምን መልክ ይኑረው ለሚለው የተለያዩ ሃሳቦች ሊኖሩ ችላሉ::  የሚከተለው አንድ አማራጭ ሊሆን ይችላል ብዬ ባለ አስራ ሶስት ነጥቦችን አስቀምጫለሁ::

1ኛ  43 አባላት ያሉት ጊዚያዊ ምክር ቤት ይመሰረታል:: በሚከተለው ቀመር የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካይች ይልካሉ:: ገዢው የብልፅግና  ፖርቲ አንድ ሶስተኛውን መቀመጫ ይይዛል:: የፖለቲካ ፖርቲዎች ብቻ ያካተትኩት  ነገሮች ሊቀላጠፊ ይችላሉ ከሚል ነው:: የሲቪክ ማህበራት የሃይማኖት ድርጅት ወዘተረፈ እየተባለ ፕሮሰስ ማብዛት ነገሮችን ማጏተት ነው የሚሆነው::

15 ከብልፅግና  ፓርቲ

2 ከኦነግ

2 ከኦፌኮ

2  ከህወሃት

2 ከአብን

2 ከኢዜማ

2 ከህብር

2 ከመኢአድ

2 እናት

2 ነፃነት

2 ኢሶዴፖ

2 ባልደራስ

2 አረና

2 ኦብነግ

2 አዴሃን

2ኛ ዶር አብይ አህመድ ይለቃል:: ጡረታ ይወጣል::

3ኛ ከምክር ቤቱ  አባላት ለአንድ አመት ጠቅላይ ሚኒስትር ይመረጣል:: በየአመቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ይቀየራል::

4ኛ  ምክር ቤቱ በጠቅላይ ሚኒስትር አቅራቢነት ካቢኔ ይመሰርታል:: የካቢኔ አባላት  ከምክር ቤት ውጭ በብቃትና በሞያ ይሰየማሉ:: ከአንድ አመት በላይ ሊያገለግሉ ይችላሉ::

5ኛ   ጊዚያዊ መንግስቱ ከሶስት አመት በላይ አያገለግልም::በሶስት አመት ውስጥ ምርጫ ያደርጋል::

6ኛ   ፖርላማውና የክልል ምክር ቤቶች ይፈርሳሉ:: በዞን  ያሉ ምክር ቤቶችና አስተዳደሮች እንዲቀጥሉ ይደረጋል::

7ኛ   የክልል ልዩ ሃይሎች በአገር መከላከያ ስር ሙሉ ለሙሉ እንዲጠቃለሉ ይደረጋል::

8ኛ   የፌዴራል የመንግስት መግባቢያ ቋንቋ አማርኛ ሆኖ ይቀጥላል:: ሁሉም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የፌዴራል የስራ ቋንቋ ይሆናሉ:: ዜጎች በሚናገሩት ቋንቋ መንግስታዊ አገልግሎት የማግኘት መብታቸው ይጠበቃል::

9ኛ  በሁሉም አገሪቷ አማርኛና እንግሊዘኛ ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ እንደ ትምህርት ይሰጣል::ሶስተኛ ቋንቋ ወላጆች የመረጡት ይሁን የወረዳ የዞን አስተዳደር የመረጡት በግዴታ ይሰጣል:: ሶስተኛ ቋንቋው የአገር ውስጥ ወይንም የውጭ አገር ቋንቋ ሊሆን ይችላል::

10ኛ  ጊዜያዊ መንግስቱ በአገሪቱ መረጋጋት እንዲመጣ መፈናቅሎች ግድያዎች እንዲቆሙ ዜጎች በነፃነት በሁሉም የአገሪቷ ክፍል መንቀሳቀስ እንዲችሉ ማድረጉ ላይ ተቀድሚው ስራው ይሆናል::

11ኛ   ፍርድ ቤት: መከላከያ: ፖሊስ: የመንግስት ሜዲያ: ምርጫ ቦርድ  ገለልተኛ ሆነው እንዲዋቀሩ ያደርጋል::

12ኛ  ፍትሃዊ በሆነ መልኩ የህዝብ ቆጠራ ያከናውናል::

13ኛ የህገ መንግስት ማሻሻያ ምክክሮች ያደርጋል:: አዲስ ህገ መንግስት እንዲረቅ ወይም ያለው እንዲሻሻል  ያደርጋል::

Filed in: Amharic